• የሥነ ጽሑፍ ሰዎች እና ሥራዎቻቸው (Ethiopian Literary Giants and their Works)

    ልብ ወለድ፣ የተውኔት ድርሰት እና ጋዜጠኝነት በኢትዮጵያ (1850-1960ዎቹ)

    Novel, Play and Journalism in Ethiopia (1850-1960’s)

    ሀብታሙ ግርማ ደምሴ ሐምሌ 2011 ዓ.ም ጅግጅጋ፣ ኢትዮጵያ

    Author of the Book Habtamu Girma

    ሁለተኛ ዕትም በገበያ ላይ!

    This book is Available for sale on:

    ethiomereb.com or http://www.lulu.com/shop/habtamu-girma-demiessie/ethiopian-literary-giants-and-their-works-novel-play-and-journalism-in-ethiopia-1850s-1960s/paperback/product-24187792.html

    ስለ መጽሐፉ አጠቃላይ

    የመጽሐፉ ርዕስ፦ የሥነ ጽሑፍ ሰዎች እና ሥራዎቻቸው
    ንዑስ ርዕስ፦ ልቦለድ፣ የተውኔት ድርሰት እና ጋዜጠኝነት በኢትዮጵያ (1850-1960ዎቹ)
    ደራሲ፦ ሀብታሙ ግርማ
    ግምገማ፦ ሚለር ተሾመ (በጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ የሥነ ጽሑፍ መምህር)
    የገጽ ብዛት፦ 319
    የመጽሐፉ መጠን (ኢንች)፦ ወርድ 6 ፣ ቁመት 9
    ኮፒ ራይት፦ የኢፌዲሪ የአእምሮ ንብረት ጽ/ቤት፣ 2008 ዓ.ም


    ስለመጽሐፉ አጭር ግምገማ (ሚለር ተሾመ፣ በጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ የሥነ ጽሑፍ መምህር)

    ይህ መጽሐፍ ኢትዮጵያዊ ብዕረኞች በጸሐፊነት፣ በጋዜጠኝነት እና በተለያዩ መንግስታዊ ሹመቶች በዘመናዊ የኢትዮጵያ ሥነ ጽሑፍ፣ ጋዜጠኝነት እና አስተዳደራዊ ታሪክ ያበረከቱትን ፈርጀ ብዙ ሚና ያሳያል፡፡ በዋናነት የጸሐፊነት እና የጋዜጠኝነት ጣምራ ተግባር በየዘመኑ ማህበራዊ-ፓለቲካዊ አውድ ያሳረፈውን ተጽዕኖ በጸሐፍቶቻችን ግለ-ታሪክ አጮልቀን እንድናይ ይረዳናል፡፡ በግለ-ታሪኩ የተካተቱት ጸሐፍት መብዛታቸው እና በተደራጀ መረጃ የተዋቀረ መሆኑ መጽሐፉን ልዩ ያደርገዋል፡፡ በውስጡ የሀገራችን ዘመናዊ የሥነ ጽሑፍ እና የጋዜጠኝነት ሙያ የታሪክ ቅኝት ተካቷል፡፡መጽሐፉ በዘመናዊ የኢትዮጵያ ታሪክ የጸሐፊነት እና የጋዜጠኝነት ሙያ ፈርጦችን ማወቅ፣ መመራመር እና ማጎልበት ለሚሹ ትጉዋን የምስራች ነው፡፡

    ማውጫ (Content)

    ክፍልአንድ፦ ሥነ ጽሁፍ በኢትዮጵያ

    1.1.የኢ-ልቦለድ እና ልቦለድ ሥነ ጽሑፍ በኢትዮጵያ

    1.2.የተውኔት ድርሰት በኢትዮጵያ

    1.3.ጋዜጠኝነት በኢትዮጵያ

    1.3.1.የህትመት ሚዲያ አጭር ቅኝት

    1.3.2.የኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ አጭር ቅኝት

    1.4.የአማርኛ ቋንቋና ሥነ ጽሁፍ ጥናትጨበኢትዮጵያ

    1.5.የኢትዮጵያ መሪዎች እና መጻህፍቶቻቸው

    ክፍልሁለት፦ ታላላቅ ኢትዮጵያዊያን የስነ ጽሁፍ ሰዎች አጫጭር የህይወት ታሪክ

    አለቃ ታዬ ገብረማርያም፣ ነጋድራስ ገብረ ህይወት ባይከዳኝ፣ ፊት አውራሪ ተክለሀዋርያት ተክለማርያም፣ ቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ንጉሴ፣ ከበደ ሚካኤል፣ አሀዱ ሳቡሬ፣ መንግስቱ ለማ፣ ጳውሎስ ኞኞ፣ አቤ ጉበኛ፣ ነጋድራስ አፍወርቅ ገብረኢየሱስ፣ ራስ ቢትወደድ መኮንን እንዳልካቸው፣ ሮማነወርቅ ካሳሁን፣ ብላቴን ጌታ ህሩይ ወልደስላሴ፣ ኢዩኤል ዮሀንስ፣ ነጋሽ ገብረማርያም፣ ብላቴንጌታ መርስኤሀዘን ወልደቂርቆስ፣ ስንዱ ገብሩ፣ ሀዲስ ዓለማየሁ፣ መስፍን ሀብተማርያም፣ ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድህን፣ ብርሃኑ ዘሪሁን፣ ዳኛቸው ወርቁ፣ በዓሉ ግርማ፣አያልነህ ሙላት፣ ስብሐት ገብረእግዘአብሄር፣ ገብረክርስቶስ ደስታ፣ ደበበ ሰይፉ፣ ማሞ ውድነህ፣ ተክለጻድቅ መኩሪያ፣ ሀይሉ ገብረዮሐንስ(ገሞራው)

    መቅድም (Preface)

    ሥነ ጽሑፍ በእንግሊዝኛ ቋንቋ literature የሚለው አቻ የአማርኛ ቃል ነው። የተጻፈ ነገር ሁሉ ሥነ ጽሑፍ ነው ማለት አይቻልም። ሥነ ጽሑፍ የገሃዱን ወይም የምናባዊውን አለም ሁነቶችን በጽሑፍ ወይም ሥነ ቃል በጥበብ መግለጽ ማለት ነው። ሥነ ጽሑፍ ልቦለድ፣ ሥነ ግጥም፣ የተውኔት ጽሁፍ እና ኢ-ልቦለድ በሚል በአራት ዘርፎች ይከፈላል። ምናባዊ ትርክት (Imaginative Literature) ልቦለድ፣ ሥነ ግጥም እና የተውኔት ድርሰት ያካትታል። በኢ-ልቦለድ (Non-fiction) ዘርፍ የሚካተቱ የሥነ ጽሁፍ ውጤቶች የዜና ዘገባ (News Reports)፣ የዳሰሳ ጽሁፍ (feature article) ፣ የግለ ታሪክ (biography) ፣ የታሪክ ዘገባ (historical accounts) ሊሆኑ ይችላሉ።
    ሥነ ጽሑፍ ከጥበባዊ ፋይዳዋ ባለፈ በየዘመኑ የህዝብን አኗኗር፣ አስተሳሰብ፣ ባህልና ወግ፣ በአጠቃላይ የማህበረ ፖለቲካ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ሁነቶችን ከትባ ለትውልድ የምታስተላልፍ የታሪክ ማህደር ጭምር ናት። በአጠቃላይ ሥነ ጽሑፍ ህዝብን ከማሳወቅና ከማንቃት የማይተካ ሚና አላት።
    ስለሆነም መንግስት የሥነ ጽሑፍ ዘርፍ ልማት ከሌሎች ልማቶች እኩል ትኩረት መስጠት ያሻዋል። ከዚህ አንጻር ህዝብ የመጻፍና የማንበብ ክህሎት ብቻ ሳይሆን ልምድም ጭምር እንዲያዳብር ምቹ ሁኔታዎች መፈጠር አለባቸው። ነጋድራስ ገብረ ህይወት ባይከዳኝ <መንግስትና የህዝብ አስተዳደር> በተሰኘው መጽሀፋቸው እንደጻፉት ህዝብ እንዲያውቅና እንዲነቃ ማድረግ ጥቅሙ ለህዝቡ ብቻ ሳይሆን ለራሱ ለመንግስትም ጭምር ነው፡-
    ለአስተዳደር የሚመችና አርነት ያለው ህዝብ ጤናማ የህዝብና መንግስት ግንኙነት እንዲኖር መሰረት ነው:፤ ያልሰለጠነ ህዝብ መብትና ግዴታውን ስለማያውቅ ለማስተዳደር አይመችም፤ምክንያቱም ከንግግርና ውይይት ይልቅ ጦርነት ይቀናዋልና ነው።ስለሆነም የመንግስት ተቀዳሚ ተግባር ሊሆን የሚገባው ህዝቡ እንዲነቃና እንዲሰለጥን ማድረግ ነው።
    በተለያዩ መስኮች ታሪካቸው ሊወሳ፣ ገድላቸው ሊነገር ከሚገቡ የአገርና ህዝብ ባለውለታዎች መካከል ኢትዮጵያዊያን ጸሀፍት ዋነኞቹ ናቸው፡፡ በተለያዩ የዘመን ማዕቀፍ ብቅ ያሉ ጸሀፊያን የቀደመውን ትውልድ የፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ ማህበራዊና ባህላዊ ከፍታና ዝቅታ መዝግበው ያቆዩ፣ የዛሬን ዕውነቶችን ከትበው ለቀጣይ ትውልድ ያኖሩ የታሪክ ነጋሪዎችም ጭምር ናቸው።
    ጸሀፊያኑ በስራዎቻቸው ህዝብን ለማስተማርና ለማንቃት ብዙ ዋጋ ከፍለዋል፤ ራሳቸው እንደ ሻማ ቀልጠው ለህዝብ ብርሃን ሆነዋል። ታዲያ እነዚህን የሲቪል ጀግኖቻችንን ምስጋና መንፈግ አሉታዊ ተጽዕኖው ትውልድ ተሻጋሪ ነው፤ ዛሬ ላይ ሆነው ነገን እየሰሩ ያሉ ተተኪ ጸሀፍት ተነሳሽነት የሚጎዳም ጭምር ነው፤ የነገውን ትውልድ መሰረት ማሳጣት ነው፤ ይህም በታሪክ የሚያስወቅስ፣ ከሞራል አኳያም ወንጀል ነው።
    ስለሆነም የአገርና የህዝብ ባለውታ ለሆኑ ጸሀፊያንና ስራዎቻቸው እውቅና ከመስጠት ባለፈ መጪው ትውልድ እነዚህን ጀግኖች እንዲያውቅ ማድረግ የሁሉም ኢትዮጵያዊ የሞራል ግዴታ ነው፡፡ ያለውን የሰጠ ንፉግ አይባልም እንዲሉ በዚህች መጽሀፌ በስነ ጽሁፍ ዘርፍ ፈር ቀዳጅ የሆኑ ኢትዮጵያዊያንን ለመዘከር ያደረግሁት ጥረት ይህን የዜግነት ግዴታዬን ለመወጣት እንጂ ልዩ የሥነ ጽሁፍ ችሎታ ኖሮኝ እንዳልሆነ አንባቢያን እንዲገነዘቡልኝ እፈልጋለሁ።


    መግቢያ (Summary)

    በዚህ መጽሀፍ በልቦለድና ኢ-ልቦለድ ሥነ ጽሑፍ ፈር ቀዳጅ የሆኑ፣ምቹ ባልሆነ ሁኔታ ውስጥ ሆነው ለዘርፉ እድገት የራሳቸውን ሚና የተጫወቱ የሠላሳ አንጋፋ ኢትዮጵያዊያን የህይወት ታሪክና ስራዎቻቸው በአጭሩ ቀርቧል። በመጽሀፉ የተካተቱት የሥነ ጽሁፍ ሰዎች በርካታ የሚያመሳስላቸው ጉዳዮች አሉ፤ ከዚህ አንጻር የልቦለድና የተውኔት ድርሰት እንዲሁም ጋዜጠኝነትን በሁለገብነት የሚከውኑ መሆናቸው ዋነኛው ነው።
    ይህን መጽሀፍ ለማዘጋጀት ከሰባ በላይ መጽሄቶችና ጋዜጦች፣ መጽሀፍት፣ የጥናት ውጤቶችና ጆርናሎች፣ የቴሌቭዥንና የሬዲዮ ፕሮግራሞች፣ ድረ ገጽ መረጃዎችን እንዲሁም ሌሎች የህትመት ውጤቶችን እንደ ማጣቀሻ ወስጄአለሁ። ከእነዚህ የህትመት ውጤቶች ጸሀፊያኑ ራሳቸው ስለ ስራዎቻቸውና የህይወት ጉዟቸው በተለያዩ ጊዜያት ያደረጓቸውን ቃለ መጠይቆች፣ ሌሎች ጸሀፊያን በስራዎቻቸው ዙሪያ ያጠናቀሯቸው ትንታኔዎች ለማየት ሞክሬአለሁ። በግሌ ያነበብኳቸውን መጻህፍት ይዘት በራሴ አረዳድ በጥቂቱም ቢሆን ለመጻፍ ጥረት ባደርግም ቴክኒካዊና ጥንቃቄ ማድረግ ስለሚያሻ በአብዛኛው ግን የስነ ጽሁፍ ባለሙያዎች የሰጧቸውን ሂሶችና ትንታኔዎችን ማካተትን መርጫለሁ። ለዚህም ምክንያቴ አንደኛ ሁሉም መጻህፍትና ተውኔቶችን የማንበብና የማግኘት ዕድሉ አልነበረኝም፤ ሁለተኛና ዋናው ጉዳይ ይህን ለማድረግ ራሱ የሀያሲነት ሙያን ይጠይቃልና በማላውቀው ሙያ ገብቼ አንባቢን ማሳሳት ስለሌለብኝ ነው።
    የመጽሀፉን ጠቀሜታና አስፈላጊነት አንባቢያን የሚመዝኑት ቢሆንም እኔ ግን ይህን መጽሀፍ የማሰናዳት አስፈላጊነት ቢያንስ ከአራት አቅጣጫዎች ለማየት ችዬአለሁ። በቅድሚያ ትናንትን ያሳዩንና ለዛሬ መሰረት የጣሉ ፈር ቀዳጅ ደራሲያንና ጋዜጠኞችን የህይወት ታሪክ እንዲህ ማዘጋጀቴ በትንሹም ቢሆን ለስነ ጽሁፍ አለም ዕድገት ላበረከቱት ውለታ ማስታወሻ እንዲሆን በማሰብ ነው። ሁለተኛ የኢትዮጵያን ጸሀፍትን የግል የህይወትና የስራ ጉዞ መርምሮ እንደዚህ ማዘጋጀቱ አንባቢያን ከጸሀፍቱ የግልና የስራ ህይወት ሊማሩ የሚችሏቸው በርካታ ፍሬ ነገሮች አሉ ብዬ ስለማምን ነው። ሌላው ጉዳይ በተለያዩ ጊዜያት የጸሀፊያንን የስራና የህይወት ታሪክ በጋዜጦች፣ በመጽሄቶችና በመጽሀፍት ለመዘከር በተደረጉ አንዳንድ ጥረቶች የመረጃዎች መጣረስና መዛባት በስፋት ይስተዋላል። በዚህ መጽሀፍ እነዚህን ጉድለቶች ለመሙላት ተሞክሯል። ከሁሉ በላይ ግን ይህ መጽሀፍ የደራሲያኑን ስራዎችን ይዘትና ጥልቀት፣ እንዲሁም የህይወት ጉዞ በስፋት ለመዳሰስ ለሚፈልጉ ሌሎች ጸሀፊያን ምናልባትም እንደመነሻ ይሆናል የሚል ጽኑ እምነት አለኝ።
    ስለ ደራሲያንና ስራዎቻቸው ከማንሳት በፊት በተለያዩ የጊዜ ማዕቀፎች የስነ ጽሁፍ ዘርፍ ከባቢን ማሳየት ተገቢነቱ አያጠራጥርም። ይህም መጽሀፉን ምሉዕ ከማድረግ ባለፈ የዘርፉን ተግዳሮቶችና መልካም አጋጣሚዎች በማሳየት ጸሀፊያኑ ያለፉበትን መንገድ ሊጠቁመን ይችላል፡፡ በዚህም በመጽሀፉ የመጀመሪያ ክፍል በዋናነት ከ1850ዎቹ እስከ 1960ዎቹ መጨረሻ ባለው የዘመን ማዕቀፍ በኢትዮጵያ የልቦለድና ኢ-ልቦለድ ስራዎች፣ የተውኔት ድርሰትና ጋዜጠኝነት ዙሪያ አጭር ቅኝት ለማቅረብ ሞክሬአሁ፡፡
    ሠናይ ንባብ!
    ሀምሌ 19 ቀን 2010 ዓ.ም
    ጅግጅጋ፤ ኢትዮጵያ

  • GET NATURE RIGHT!

    WHY UPHOLDING NATURAL LAWS SO IMPORTANT?

    Habtamu Girma, Lecturer at Jigjiga University, Department of Economics.

    The World is Not Fair

    When I listen to the calls of nature, I hear a scream from all creatures. May be, we feel and hence lend our ears to the human grief only; the suffering of other life is however far from the table of discussions often times. However, unable to speak out their suffering in words doesn’t mean the fauna and flora are passive; a deeper look into the world entails they rather are showing their sufferings in action, calling for a fair world where no life flourishes at the expense of the other; a world which is just not only for humankind, but also for all life; calling for pretty fair allocation of resources in a way that may not affect the health of other living things: big or small, born or unborn, of all the present and future generations.

    In Search of a Fair World……

    Where is a fair world for all creatues- be it human kind or other lifes, the fauna and flora? Where is that land of universal happiness and prosperity? Where is that part of world in which justice and fairness prevailed? Can we model for a utopia that provides us with ‘yes’ for all these quests; or remains a mere wish? If we can, how dear (cheap) is the cost of securing that dream land? Indeed, these are not mere questons at all; nor do make one with this point ideal. I am optimistic about a utopia, where joy, hope and prosperity in abundance. As our utopia is our common land, everyone shall have a say in the whole process of towards its construction. In this article, I would try to put forward my views on the essence of modelling a utopia where fair and just order prevails; also suggestions on the possible ways & means and preconditions required in pursuit of that dream land is made.

    Dreaming for a Utopia

    Once again, I would say dreaming for a utopia free of social, economic, political and environmental woes is not mere wish. Indeed, realizing that dream requires to understand two interrelated elements: the first is to understand nature: its rules and working principles, which shall be taken a necessary condition; and the second is one`s readiness to sense life to the fullest, what I preferred to be considered a sufficient condition. The former takes only endowing a deep sense of affection and readiness to lending the required time and energy to make inquiries into nature and its laws. Such a critical look into nature enables to draw a clear depictions of nature: about its purpose, governing rules, and how it works in general. The latter requires lust and determination to practice the dictations of nature and bowing down to its rules, which should be considered as an essential virtue of human being. All in all, a path that takes to our utopia requires us to understand nature; in this regard, two issues are worth remembering: re-defining what life means; and re-statement on civilization.

    Nature a Healer!

    What is nature all about? If I may to speak about nature is in a single word, I respond ‘nature as a reality’. Nature is a supreme force meant to keeping the healthy workings of the world, where all life fetches fair share from natural peace. The fact that understanding nature and natural order requires an in-depth look into the visible and invisible world begs the fact that humankind, the only animal with a reasoning power, is endowed with an ability to understand nature and hence privileged with all power and wisdom that enables it control its environment, and govern all other life on earth. When human kind is privileged with these powers, it is not without some strings attached, that is readiness to learn on nature and natural order, which I rather to dub as one virtue of human characters.
    Through its interrelated and sophisticated rules and principles, nature defines and governs the whole aspects of life, of all creatures. The most important governing rules of nature are: ‘extremes are bad’, ‘self-interest is inherent in human nature’, ‘believe in natural justice’ and ‘existence of every creature (species) is for purpose’.
    In our drive towards that dream land, where all life can live in harmony, all it takes is to understand nature, and lend our respect to its rules. This in turn takes redefining life. Lets for a while, ask ourselves: What life really mean for us; if we are living life to the fullest. No doubt that there is no a commonly shared answer, and it is highly likely that at least every one of us come up with a unique solutions to these problems. If I am supposed to say mine, I say that ability to breathe in and out do not justify one as alive. I understand living as the ability to sense and respond to our feelings: to be able to smell the fragrant or bad odor; to see not only the bold, also the tiny, even the invisibles. In its breadth and width, Life is to cry when one is supposed to cry; to laugh with what makes one laughter; to shout on what one considered as unfair, to suggest for right when one feel an action is wrong, and ultimately to be a voice for a voiceless. I call upon for a revision on the conventional life-death definition, which considers ability to inhale and exhale of oxygen and carbon dioxide respectively. For me, alive are those who are genuine for their heart beat. In alternative words, living is to show a will to accept the reality; understand nature and its rules. It is only when we are in such state of mind, meaning when are really alive, that we make inquiries on the nature and naturalism, and better understand the rules of nature. People are not the same in their understanding on nature, though they are equally endowed with a tool to do so, a reasoning power. As such, peoples state of living shall be stated in terms of degrees. Considering life and death as a ceiling, we have to define other states of living, depending on the extent of ones intelligence over nature and naturalism, the level of ones courage to live by the rules and principles of nature.
    Human`s control over its environment, which we call it civilization, is nothing but understanding nature and abided by natural order. The right parameter to rely on to rank people in terms of intelligence and societies in terms of degree of civilization is the extent of intimacy they developed with nature.
    Disrespect to the rules of nature is the mother of all woes, in all departments of life: social, economic, political, and ecological at all levels. So we can cleanse ourselves from all these evils once we get nature right: show the will and courage to live by natural laws.

    Upholding Natural Order: Way for Prosperous Life

    Social chaos that filled our world would get a cure by understanding the principles of nature. The most important rules of nature that appeals in this respect are: ‘extremes are bad’, and ‘natural justice’. The former calls one to be moderate in his social transactions; while the latter connotes that everyone is rewarded based on his/her effort. By offering incentives and courage to behave in a modest and consistent manner, surrendering oneself to ‘extremes are bad’ balances our intra-personal as well as inter-personal relations. By invoking for ‘tit-for-tat’, and the principle of “do not do anything on others what you yourself dislike to happen on you”, belief in ‘natural justice’ is a force behind shaping human conduct as it helps develop moral and ethical values, which are paramount in curbing social problems like jealousy, malfunctioning & corruption, practices of stealing & robbery, and other social malades.
    Designing the proper economic strategy that leads to prosperity has for long been controversial, even today. An economic policy that appreciates the very nature of humankind is something our world starved of. Human being has both cooperative and competitive natures; yet it is natural that the competitive force outweighs the cooperative force, particularly in economic transactions. The proper economic relation is therefore the one which acknowledges and hence appreciate the competitive nature of people. Economic relations built on the premises that deny this essential element deny the prosperity that human kind deserves.
    Alternative modals of production relations we know in history: collectivism, slavery, feudalism and socialism failed to work, in a sense of bringing about the welfare of the mass, for their philosphy was divorced from the inherent nature of human kind. By requiring people to be selfless, socialism (communism) underestimated and crushed the competitive force inherent in human nature, and that explains the collapse of socialism. Capitalism survives as a leading economic philosophy, because it acknowledges the most defining natural law in economic transactions, which is self-interest. Built on the notion of self-interest, capitalism may seems to have acknowledged the psychology of human kind. However it is undeniable that the actual working of capitalism often passes the natural limit of self-interest (self-love), a rational selfishness, which I mean is devoid of greed. The whole evils of capitalism arises due to corrupt understanding of individualism.
    The political system that respects the dignity of people, the one which promotes the principles of free speech and thought, and which entertains the rule of the majority and defends the rights of minority, is the natural political system. Any deviation from that, or a political philosophy which denies the very nature of people, that is self-love, manifested in the lust for dignity and respect, is the one which shall be condemned for making peace scarcer, and human grief abundant.
    Scientists put ecological imbalance as a ‘root cause’ of environmental problems. Yet, we can move one step behind to explore “why environmental crisis?”, and the answer lies in disrespect for natural order: ‘existence of every creature (species) is for purpose’. Upholding this principle connotes that any infliction against a single species is an infliction against all life, which in turn calls for environmental protection and hence ecological balance.
    Once we Get nature triumph, once we accept and bow-down to natural laws, once we accept the reality, then we are on the right path to our utopia, where joy, hope and prosperity in abundance in all aspects of life: be it social, economic, political and ecological.

  • የኢትዮጵያ ችግር የአመል ችግር እንጂ ሌላ አይደለም!

    ሀብታሙ ግርማ መስከረም 3/ 2011 ዓ.ም
    አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

    መግቢያ

    የጽሑፌ ጭብጥ የጽሑፉ ርዕስ ነው። ዛሬ በውድ የኢትዮጵያ ወጣቶች ደም ስንናፍቀው የኖርነውን የነጻነት አየር መተንፈስ በጀመርንበት ወቅት የኢትዮጵያ ህዝብ እርስ በርስ ለመነቋቆር እና ለመበጣበጥ የሚነሳበት ምክንያት የለውም፤ ነገሩ የፖለቲካ አጀንዳ ልዩነት(ቢኖር እንኳ በንግግር መፍታት ይቻላል) ሳይሆን የአመል ነው። የአመል ችግር የሚለውን የሚጠቀልል የአማርኛ ቃል የቅንነት ችግር (Lack of integrity) ነው።
    ቅን አለመሆናችን ለብዙ መከራ ዳርጎናል፤ ከቤተሰብ ጀምሮ እስከ አገራዊ ችግሮቻችን መነሾ ናቸው የምላቸው ምክንያቶች የዚሁ ውጤት ናቸው።

    የቅንነት ችግር ምልክቶች

    የቅንነት ችግር ምልክቶች የሚከተሉት ናቸው፦
    እውነትን ከሐሰት፤ ትክክለኛውን ከስህተተኛ ለመለየት የመንፈስ፣ የሞራልም ሆነ የአእምሮ ዝግጁነት ማጣት፣
    በስሌት ሳይሆን በስሜት መነዳት፣
    ለበረታው ዕውቅና ከመስጠትና በመንፈሳዊ ቅናት( rational selfishness) ተነሳስተን ከስኬቱ ሂደት ለመማር ከመሞከር ይልቅ ስኬቱን ለማሳነስ መሞከር፣
    ብልጣብልጥነት፣ ጮሌነት እና የድል አጥቢያ አርበኝነት ባላጠቃን ነበር

    እኛ ኢትዮጵያውያን ቅንነት ቢኖረን ኖሮ……..

    በህይወት መስመራችን ጉዳያችን የሆነን ነገር የምናውቅ፣ በመሆኑም አላስፈላጊና ጥቃቅን የሆኑ ነገሮችን እንደ ጉዳይ ወስደን ራስ በራሳችንን ባላደከምን፣ የምናደርገው ነገር ሁሉ በምክንያት በሆነ ነበር፤ የድርጊቶቻችን ውጤት አንዱን ይዞ አንዱን መጣል አይነት ሆኖብን ለመንግስት ብቻ ሳይሆን ለፈጣሪ እንኳ አስቸጋሪ ህዝቦች ባልሆን ነበር፤ ለተንሸዋረረ የታሪክ አረዳዳድ ባልተጋለጥን ፣ በመሆኑም የረጅም ዘመን ታሪካችን ለአንድነታችን መሠረት የሆኑ እጅግ በርካታ በጎ ሁነቶችን ያዘለ ቢሆንም ይህ የታሪክ እውነት ደብዝዞ በአንጻሩ ያለፈው በጎ ያልሆነው የታሪካችን አካል ባልደመቀ ነበር።
    በታሪክ ሂደት ያሳለፍነው በርካታ መልካም እንደነበር ሁሉ መልካም ያልሆኑ ግንኙነቶች እንዳሳለፍን እንረዳ ነበር፤ በመሆኑም የምንወዳት እና የጋራ ቤታችን የሆነችው ኢትዮጵያ የምንላት አገር ህዝቦቿ በተለያዩ ምክንያቶች (ኃይማኖታዊ፣ የማንነት፣ ራስን በራስ የማስተዳዳር ወዘተ….) በተለያዩ ወቅቶች በአገራዊ እና አለማቀፋዊ ገፊ ምክንያቶች እርስ በርስ የተዋጉ፣ አንዱ ሌላውን ያስገበረበት ሁነቶች በርካታ መሆናቸውን በአንድ በኩል የመካድ በሌላው በኩል የማጉላት አዝማሚያ የፖለቲካችን መዘውር (pillar) ሆኖ ባልተቸገርን ነበር። ዛሬ ላይ በጎ ያልሆነውን የታሪካችን አካል እና(ወይም) ወካይ ምልክቶቹን ማንሳታችን ተገቢነቱ ካለፈው ስህተታችን ለመማር እንጂ ለመነታረክ ፣ ለመበሻሸቅ፣ የአሸናፊነት ወይም የተሸናፊነት መንፈስ በማስረጽ ባልከፋፈለን ነበር፤
    በመሆኑም ዛሬ ላይ ይህን በጎ ያልሆነ የታሪክ አሻራ ጠባሳ ሰለባ ያልሆነ የኢትዮጵያ ህዝብ አካል የሆነ ብሔር፣ የሐይማኖት እና የፖለቲካ ቡድን አለመኖሩ፣ በዚህም የኢትዮጵያ ህዝብ የእነዚህ የማህበረብ ክፍሎች(ህዝቦች) ድምር መሆኑን ተረድተን፣ የመጥፎ ታሪካችን ሰለባ የነበሩትን ወገኖቻችንን የሚያበሳጩ፣ ሰቆቃቸውን የሚያስታውሱ ምልክቶች ለሌላኞቻችን የድል አድራጊነት፣ የአሸናፊነት፣ ምልክት ከማድረግ በተቆጠብን ነበር ፤ በአጠቃላይ ታሪካችን የመማሪያ ሳይሆን መጥፎ የታሪክ አሻራችን አገርሽቶ ሌላ መጥፎ ታሪክ ለመጭው ትውልድ ለሚያወርሱ እኩይ ድርጊቶች የሚጋብዝ፣ ትልቅ የተስፋ ጮራ የፈነጠቀውን የለውጥ ሂደት የሚቀለብስ፣ ሲከፋም የጋራ ቤታችን የምንላትን ኢትዮጵያ ምኞት ብቻ እንዳትሆን ትልቅ ስጋት ባልሆነ ነበር።

    ቅንነት ቢኖረን ኖሮ……..

    የአገር አንድነት እና የሉዓላዊነት ጉዳይ ጨምሮ በእለት ተዕለት ግንኙነቶቻችንን የምንወያየው እና የምንከራከረው ፋይዳ ስላለው ጉዳይ ይሆን፣በእንቅሰቃሴዎቻችን ሁሉ ትልቁን ምስል ባልተጋረደብን ነበር፤
    በቅርብ ታሪካችን አይተን የማናውቃቸው እንደ ለማ መገርሳ፣ ገዱ አንዳርጋቸው፣ አብይ አህመድ፣ ደመቀ መኮንን፣ ሙፈሪሃት ከማል እና ሙስጠፌ መሀሙድ ኡመር አይነት ጥሩ መሪዎች አግኝተን በነቢብ እየደገፍናቸው በገቢር ግን እየወጋናቸው መሆኑን መገንዘብ ይቻለን ነበር፤ መልካም አመራራቸውን ለመደገፍ ከመጣር ይልቅ በየዕለቱ የቤት ስራ ባልሆንባቸው ነበር።
    ኢትዮጵያዊያን የቅንንነትን እሴቶችን እሴቶቻቸው በማድረግ ራሳቸውንም ሆና አገራቸውን ከጥፋት ይታደጉ ዘንድ ብቸኛው አማራጫቸው ነው።

    አዲሱ ዓመት ሁላችንም ቅንነትን የምንለማመድበት ዘመን ይሆን ዘንድ እመኛለሁ።

    ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቧን ይባርክ፤ አሜን!!!

  • ከኢትዮጵያዊነት የስነልቦና ውቅር የተፋታው የህወሃት የፖለቲካ መስመር !!!

    ሀብታሙ ግርማ፣ በጅግጅጋ ዩኒቨርስቲ የኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል መምህር

    ማስታወሻ:- ይህ መጣጥፍ ነሐሴ 1 ቀን 2011 ዓ.ም በሪፖርተር ጋዜጣ ለህትመት ቢበቃም፣ ጽሑፉ የተዘጋጀው ከአመት በፊት ነበር። መጣጥፉ በይዘቱ የህወሃትን የፖለቲካ አስተዳደር ዘይቤ (system of political governance) በርዕዮተ ዓለማዊ መነጽር በወፍ በረር መገምገም ነው፤ በዋናነትም የህወሃት መራሹ ኢህአዴግ አመራሮች የፖለቲካ ስብዕና መሠረታዊያንን መጠቆም ነው። መጣጥፉን በዚህ ወቅት ለአንባቢ የማድረሱ ዓላማ ሁለት ነው፥ አንድም ህወሃትን በማጥላላት ሳይሆን ምክንያታዊ በሆነ መልኩ ለመተቸት ነው። ሁለትም በድህረ-ህወሃት ኢትዮጵያ (Post TPLF Ethiopia) የፖለቲካ ማማ ላይ የወጣው የለውጥ አመራር ምናልባት ወጣ ገባ በበዛበት ነባራዊው የኢትዮጵያ ፖለቲካ ተሰላችቶ ለፖለቲካው ብልሽት ዘላቂ መፍትሄ ከመፈለግ ይልቅ የህወሃትን መስመር ያዋጣ ይሆን ብሎ የውድቀት ቁልቁለት እንዳይጀምር ለማሳሰብ ነው። ቅዱሳን መጽሐፍት እንደሚያስተምሩን የሰው ልጅ በክፉዎች መቅናት የለባቸውምና የህወሃትን መስመር እንዳይመኘው ምክር ቢጤ ለመወርወር ነው።

    መግቢያ

    ካለፉት 40 ዓመታት ጀምሮ የትግራይ ህዝብ የፓለቲካ ትግል እና የሥነ መንግስት ቅርጽ የሆነው ህወሃት እንዴት የትግራይ ህዝብ ነባራዊ ሀቅ ከሆነው የታሪክ፣ ባህል፣ ሥነ ልቦና እና እምነት ያፈነገጠ እንደሆነ ብዙዎች ይኮንናሉ፤ እኔም ይህን ግምገማ እጋራለሁ፡፡ የትግራይ ህዝብ እንደሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ሁሉ ለሥልጣን እና ሥነ መንግስት ያለው አመለካከት አዎንታዊ ሆኖ ሳለ ህወሃት የኢትዮጵያ ህዝብ ማዕከላዊ መንግስት ፊት አውራሪ ሆኖ በቆየባቸው ሶስት አስርት ዓመታት ገደማ ለኢትዮጵያዊያን ባዕድ የሆነ የሥነ መንግስት ፍልስፍና እና የአስተዳደር ዘይቤ እንዲከተል የሆነበት መሠረታዊ ምክንያት ምንድነው? ይህ መጣጥፍ ለእነዚህና ተዛማጅ ጥያቄዎች መልስ ያፈላልጋል።

    የትግራይ (የኢትዮጵያ ህዝብ) ታሪካዊና ሥነ ልቦናዊ መሠረቶች

    በመሠረቱ የትግራይ ህዝብ የኢትዮጵያ ሀገረ መንግስት ግንባታ እንዲሁም የፖለቲካ ግንባታ ትልቅ ድርሻ የያዘ ነው፡፡ በመሆኑም የትግራይ ህዝብ በኢትዮጵያ የአምስት ሺህ አመት ታሪክ ጉልህ ስፍራ አለው። በርካታ ጸሐፍት እና የታሪክ ሊቃውንት እንደጻፉት የኢትዮጵያ የጥንት ስልጣኔ የመንፈሳዊ ስልጣኔ ነው፤ የቁሳዊ ስልጣኔ አልነበረም። የመንፈሳዊ ስልጣኔው አሻራ የሆኑት ደግሞ ፈሪሃ እግዚአብሄር፣ የፈጣሪ መንገድ የሆኑትን ሃይማኖቶችን አለመዳፈር፣ ለህግ መገዛት፣ ሥርዓተ መንግስትን ማክበር፣ ውለታ አለመርሳት፣ ለይቅርታ እና እርቅ ዋጋ መስጠት፣ ይቅር ባይንና አስታራቂን ማክበር ከብዙ በጥቂቱ ናቸው። የተጠቀሱት መልካም እሴቶች ለኢትዮጵያ ህዝብ (ለትግራይ ህዝብ) የታሪኩ፣ የባህሉ፣ትውፊቱ፣ እምነቱ፣ መሠረት የሆኑ በአጠቃላይ የኢትዮጵያዊ ሥነ ልቦና ወይም ተክለ ስብዕና መገለጫዎች ናቸው።

    የቀደሙት የኢትዮጵያ ሥርዓተ መንግስታት…….

    በተለያየ ዘመን ኢትዮጵያን ያስተዳደሩ ሥርዓረተ መንግስታት እና መሪዎች ከፍ ሲል ከእነዚህ አትዮጵያዊ መገለጫዎች ተነጥለው የማይታይ የአስተዳደር ዘይቤ ይከተሉ የነበሩ፣ ዝቅ ሲል እነዚህን መልካም እሴቶች በድፍረት የሚጨፈልቁ አልነበሩም በመሆኑም ለህዝባዊ አንድነት መሠረት የሆኑትን የበጎ ሥነ ምግባር እሴቶች ለሆኑት መከባበር፣ መተማመን፣ መተሳሰብ ዋጋ የሚሰጡ፣የኢትዮጵያ ህዝብ ለክብር እና ኩራቱ የሚጋደል መሆኑን ጠንቅቀው የተረዱ፤ ኢትዮጵያዊ ለህገ-ህሊናው የሚገዛ፣ ሰው ወዳድ፣ ካልነኩት የማይነካ፣ ከራሱ በላይ ለእንግዳው ቅድሚያ የሚሠጥ፣ ፍርድ ሲጓደል ለምን የሚል፣ ለማህተቡ (ለእምነቱ) ሟች መሆኑን በመልካም ወስደው እነዚህን ህዝባዊ እሴቶች ሊተናኮሉ(ሊሸረሽሩ) ይቅርና የፖለቲካ ፍጆታ ወይም የፕሮፓጋንዳ መሣሪያ ለማድረግ ድፍረት አላሳዩም።
    ስልጣን የህዝብ ማገልገያ እንጂ የጭቆና መሣሪያ አይደለም የሚለውን መርህ በግላጭ ለመዳፈር አልሞከሩም፤ የማዕከላዊ መንግሥት ሥልጣን የአገራዊ አንድነት ማረጋገጫ ማህተም እንጂ በጥበብ የመከፋፈያ መሣሪያ አድርገው አልተጠቀሙም፤ በፖሊሲዎቻቸው የመንግሥት ሥልጣን የተመሪው ህዝብ በጎ እሴቶቹን እንዲጠብቅ መሠረታዊ ተቋማት የሆኑትን፣ ማለትም ሀይማኖት ቤተሰብ እና የትምህርት ተቋማትን ቢያንስ ለማዳከም ሴራ አልሸረቡም።

    ታዲያ ህወሃት ከነባራዊው ኢትዮጵያዊ አስተሳሰብ ለምን አፈነገጠ?

    ዛሬ ላይ ህወሃት መራሹን መንግስት ስገመግም ከቀደሙት የኢትዮጵያ የተለየ ሆኖ አገኘሁት። ለአንባቢ ህወሃት ከትግራይ(ኢትዮጵያ) ህዝብ ባህል፣ ታሪክ፣ ስነ ልቦና በብዙ መልኩ የሚጻረር የፖለቲካ መሥመር ይከተላል ለሚለው አስረጅ ማቅረብ ለቀባሪ እንደማርዳት ነው፤ ከዚህ ይልቅ ህወሃት ለምን እንዲህ አፈንጋጭ የአስተዳደር ዘዬ የይከተላል ብሎ ማጠየቅ ተገቢ ይመስለኛል። በእኔ ግንዛቤ ለዚህ መልሱ የሚከተለው ርዕዮተ ዓለም ነው።
    የህወሃት የፖለቲካ መሥመር አብዮታዊ ዲሞክራሲ ነው። በህወሃት ቤት አብዮታዊ ዲሞክራሲ ከአይዲዮሎጂም በላይ ነው፤ ሀይማኖት ነው። አብዮታዊ ዲሞክራሲ በእሳቤው የትኛውንም አገራዊም ሆነ ህዝባዊ ጉዳይ የመሸጋገሪያ እንጂ ግብ አይደለም። በመሆኑም የሥነ መንግስት እሳቤው መርህ መሠረት እና(ወይም) መገለጫ የሆኑት ህገ መንግስት፣ ርዕዮተ ዓለም፣ ቢሮክራሲ፣ ዲሞክራሲ፣ ፖሊሲ ወዘተ…. የታክቲክ ጉዳዮች ናቸው። በመሆኑም በህወሃት የአስተዳደር ዘመን በኢትዮጵያ ግልጽ የሆነ፣ ርዕይ ያለው፣ ስትራቴጂካዊ፣ ሳይንሳዊ፣ ተዓማኒ(legitmate)፣ የሚገመት (predictable) የህዝብ አስተዳደር መስመር እና ተቋማት እንዳይኖር አድርጓል።

    ህወሃት ለምን በህዝብ ይጠላል?

    ህወሃት በብዙ ኢትዮጵያዊያን እንዲጠላ የሆነበት ምክንያት የሚከተለው ሶሻሊስታዊ መስመር ከሰወኛ እሴቶች (human values)፣ በተለይም ከኢትዮጵያዊ እሴቶች (Ethiopian Values) በብዙ መልኩ የማይገጥም መሆኑ ነው። ይህን በዝርዝር በአዲስ መስመር ስንመለከተው
    የህወሃት የፖለቲካ ኢኮኖሚው መሠረት የኢትዮጵያን ታሪክ በማይመለከተው የማርሲስት ሌኒኒስት የበዝባዥ- ተበዝባዥ አስተምህሮ መቃኘቱ ነው።
    * ከሁሉም በላይ የኢትዮጵያን ህዝብ ስነ ልቦና በተጻራሪ ሁሉንም የህዝብ መስተጋብር በዲያሌክቲክ ቁሳካላዊነት ለመግለጽ መሞከሩና የማህበረ ፖለቲካ ኢኮኖሚ ፖሊሲዎቹ መነሻና መድረሻ ማድረጉ ነው።
    የህወሃት የሚከተለው ሶሻሊስታዊ የአስተዳደር ዘይቤ መጠራጠርንና መከፋፈልን መሠረቱ ያደረገ፣ ህዝብን ወይም የማህበረሰብ ክፍሎችን በጠላት እና ወዳጅ (friend-foe dictum) የሚከፋፍል በመሆኑ ነው።
    የህወሃት አብዮታዊ ዲሞክራሲ በሶሻሊስት አስተምህሮ የተቃኘ፣ ከግለሰብ ይልቅ ቡድንን የሚያስቀድም መሆኑ ለዜግነት እሴቶች ይልቅ ቡድናዊነትን ስለሚሰብክ ነው።
    * አብዮታዊ ዲሞክራሲ ታሪክን የሚረዳበት መነጽር ቁስ አካላዊነትን መሠረት ያደረገ (Historical Materialism)፣ የታሪክ ሁነቶችን የሚተነትንበት አግባብ ደግሞ ህዝብን በጠላት ወዳጅ የሚለያይ (Class Conception of History) መሆኑ ነው።
    * ህወሃት የሚከተለው ሶሻሊስታዊ መስመር በዘመናት ሂደት የህዝብን የማህበረ ፖለቲካ እና ኢኮኖሚ፣ ስነ ልቦና እና ተክለ ስብዕና የማዕዘን ድንጋይ ለሆኑት እንደ ባህል፣ ታሪክ፣ ትውፊት፣ እምነት፣ ሥነ ትምህርት፣ ሥነ ምግባር የመሳሰሉት እውቅና ከመስጠት ይልቅ አፈራርሶ ሶሻሊስታዊ (ቁሳዊ) ማንነትን በህዝብ ላይ ለመጫን (Mass Inclulcation of Socialist Ideals) መሞከሩ፣
    * በዚህም ሁሉንም ነገር ፖለቲካ የማድረግ ዝንባሌው ለዘመናት የፖለቲካ አይነኬ የሆኑትን ህዝባዊ (የመንፈሳዊ ወይም የሀይማኖት) ተቋማት ላይ ሳይቀር ጣልቃ በመግባት የፕሮፓጋንዳ መሣሪያ ለማድረጉ መሞከሩ ነው።

    በመጨረሻም…..

    ፈጣሪ የህወሃት ሰዎች ከአብዮታዊ ዲሞክራሲ አጥፊ መንገድ ይመለሱ ዘንድ ልቦና ይስጣቸው ዘንድ እጸልያለሁ፤ ለትግራይ ህዝብ ደግሞ (ጠ/ሚ አብይ በመጀመሪያው የትግራይ ጉብኝታቸው ወቅት ከተናገሩት፣ አፋቸውን ልዋስና) “….ከንቐደምና” ወይም “…..እንደድሯችን” የሚል መልዕክት ለመስደድ እወዳለሁ።

    ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቧን ይባርክ፤ አሜን!

  • ‘አዲስ አበባ የማን ናት?’ የሚለው ጥያቄ ኢትዮጵያን የኢትዮጵያዊያን በማድረግ ይፈታል!

    ማስታወሻ:- ይህ መጣጥፍ መጋቢት 4 ቀን 2011ዓ.ም (March 13 2019) ለንባብ በበቃው ሪፖርተር ጋዜጣ ለአንባቢያን ደርሷል። መጣጥፉ የሚያጠይቃቸው ጉዳዮች ዛሬም ያልተፈቱ ጉዳዮች ናቸው። በመሆኑም በዚህ መጣጥፍ የይዘትም ሆነ የጊዜ ጠቋሚ የቅርጽ ማስተካከያ አልተደረገም። አንባቢ ይህን ይገነዘብ ዘንድ በአክብሮት ለማሳሰብ እወዳለሁ። ጽሑፉን ከመጀመሪያው ህትመት ማንበብ ለምትሹ በሚከተለው ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ። ሰናይ ንባብ https://www.ethiopianreporter.com/article/15054


    ሀብታሙ ግርማ፣ ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ፣ የኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል መምህር


    መግቢያ

    በዚህ መጣጥፍ ሁለት ጉዳዮች ተነስተዋል፤ አንዱ የአዲስ አበባ ከተማ የባለቤትነት ጉዳይ ሲሆን ሁለተኛው ከዚህ ጋር ተያይዞ በቅርቡ ለአዲስ አበባ ነዋሪዎች ከተላለፉት የኮንዶሚኒየም ቤቶች ጋር ተያይዞ የተነሳው ውዝግብ ነው።


    አዲስ አበባ የማን ናት?

    የሰሞኑ የሶሻል ሚዲያ ጉዳይ አዲስ አበባ የማን ናት? የሚለው ነው። የአዲስ አበባ የባለቤትነት ጉዳይ መነሳቱ ስህተት የለውም። ችግሩ ኢትዮጵያ የዜጎቿ የመሆኗ ነገር እጅግ ባጠራጠረበት ዘመን አዲስ አበባ የማን ናት? ብሎ መጠየቁ የፌዝ ስለሚመስል ነው። ጥያቄው የፌዝ ነው ተብሎ ግን መልስ መስጠት አለመቻል ማብቂያ ለሌለው ሙግት እና/ወይም ጠብ ያጋልጣል። ይህ አይነት ሙግት ወይም ጠብ መንስኤም፣ ውጤትም (አሸናፊም ሆነ ተሸናፊ)፣ ማለቂያም የለውም፤ ትርጉም አልባ ነው።
    ከማህበራዊ ሚዲያዎች ትዝብቴ አዲስ አበባ የማን ናት? ለሚለው ጥያቄ መልስ የሰጡትን በሶስት ቡድን መክፈል ይቻላል።
    የመጀመሪያው በአብዛኛው አዲስ አበቤ ሲሆን፣ ይህ ቡድን አዲስ አበባ የነዋሪዎቿ ናት ይላል።
    ሁለተኛው ቡድን ከአዲስ አበባ ውጭ ያለ፣ በአመዛኙ የኦሮሞ ወገን ሲሆን አዲስ አበባ (ፊንፊኔ) የኦሮሞ ህዝብ ናት ይላል (በአዲስ አበባ የሚኖር የኦሮሞ ወገን አዲስ አበቤ ራሱን በብሔር የመግለጽ ዝንባሌ የለውም የሚል እምነት ስላለኝ ነው)።

    ሶስተኛው ቡድን አዲስ አበባ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ናት የሚለው ነው። ይህ ቡድን ቁጥሩ አነስተኛ ቢሆንም ብዙሃኑ ሀቀኛ አይደለም፤ አልያም የመንጋ ውዝግብ ሰለባ ነው። ምክንያቱም አንድ ኢትዮጵያ ባለበት አንደበቱ የአጉል ብሔርተኛነት ጩኸት ያሰማል። በእውነቱ ይህ ቡድን ኢትዮጵያን ጉዳዩ ስለማድረጉ እጠራጠራለሁ ።እንዲያውም አወናባጅ ይመስለኛል።
    ከሶስቱ ቡድኖች በተለይ በኢትዮጵያ አንድነት ስም የሚነግደው ጎራ እጅግ አደገኛ ነው፤ ምክንያቱም በአገር ቀልድ የለምና። አባላቱ በአብዛኛው የሚፈልጉትን መርጠው ማድመጥ የሚሹ፤ የሚዛናዊነት መለኪያቸው ሃሳብ ሳይሆን ግለሰባዊ ስሜታቸውን ከማስታገስ አንጻር እንጂ እንጂ ቆመንለታል ለሚሉት የኢትዮጵያ አንድነት ከማጠናከር አንጻር አይደለም። ይህ ሀይል ገሚሱ እሳት፤ ገሚሱ ቤንዘን አርከፍካፊ፣ ከፊሉ ደግሞ አራጋቢ ሆኖ አገር እየለበለበ፣ ነገር ግን ስለ ኢትዮጵያ አንድነት የሚለፍፍ ጸረ-ኢትዮጵያ ነው። እሳት ቤንዚን አነፍናፊ ነው፤ ቤንዚንም እሳት አነፍናፊ ነው። ውጤቱ ቃጠሎ ነው፤ የቃጠሎው ወላፈን እንደወረደ የሚፈጀው ደሃውን ህዝብ ነው። በእሳት እየተለበለበ እየረገፈ ያለው የኢትዮጵያ ምሰሶና ማገር ነው። ይህ የዘመናችን የኢትዮጵያ አሳዛኝ እውነት ነው።
    ከኢትዮጵያ መፍረስ አንድም የሚጠቀም የለም። አገር ሲፈርስ የእያንዳንዳችን እጣ ፈንታ አንድም ከኢትዮጰያ ጋር አብሮ መፍረስ፣ አልያም ስደት ነው። ከሁለቱ መጥፎዎች የኋለኛው የከፋ ይመስለኛል። አገር የሌለው በሄደበት ከሰው በታች መሆኑን ለመረዳት ከአገር ወጥቶ መኖር አይጠበቅም።
    በእኔ ግንዛቤ አዲስ አበባ የማን ናት? የሚለው ጥያቄ ኢትዮጵያን የኢትዮጵያዊያን በማድረግ ይፈታል።


    የአዲስ አበባ ኮንዶሚኒየም ቤቶች የውዝግብ ጉዳይን በተመለከተ…….

    የአዲስ አበባ ኮንዶሚኒየም ቤቶች የውዝግብ ጉዳይን በተመለከተ መልስ ከመስጠት ይልቅ ሁለት ተዛማጅ ጥያቄዎች መጠየቅ መርጫለሁ።
    ጥያቄ አንድ፦ ከአዲስ አበባ ወሰን 25 ኪሜ ገደማ ተገብቶ የአዲስ አበባ ቤት ማስፋፊያ ሲሰራ የድንበር ጉዳይን የወቅቱ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ጥያቄ አንስቶ ነበር? የወቅቱ የአዲስ አበባ አስተዳደርስ ይህን ጉዳይ ለምን ዘነጋው?
    ጥያቄ ሁለት፦ የተነሳው ውዝግብ የብሔር ጉዳይ ነው ወይስ የአስተዳደራዊ? ከዚህ አንጻር የቤት እጣ ከደረሳቸው 51,000 ሰዎች መካከል በብሔር መጠሪያቸው የኦሮሞ ተወላጆች የሆኑ እንዳሉ ይታመናል፤ ታዲያ ኦሮሞ በመሆናቸው ተለይተው በቤቶቹ የመኖር ዋስትና አግኝተዋል? ከሌላ ብሔር ተወላጆች የቤት እድለኞች ደግሞ በቤቶቹ እንዳይኖሩ ተከልክለዋል?

    እነዚህን ጥያቄዎች ማንሳቴ ችግሩን ለማቃለል ሳይሆን ከስሜት እና አጉል ብሔርተኝነት ወጥተን ጉዳዩን እንድንመረምር ለማሳሰብ ነው። ይህም ከውዝግቡ የሚያተርፉ አካላት የጥፋት ተልዕኮ አስፈጻሚ ወይም ተጠቂ እንዳንሆን ያደርጋል የሚል እምነት አለኝ።
    ጥያቄዎቹን ማንሳቴ ከምንም በላይ በዶ/ር አብይ የሚመራውን የለውጥ አመራር ባልፈጠረው ችግር ከመወንጀል እንድንታቀብ፣ በመሆኑም የለውጥ ሀይሉ ተከፋፍሎ እንዳይዳከም፣ ተስፋ ያደረግነው ሁሉ እንዳይጨልም በአስተውሎት መጓዝ እንዳለብን ለማስታወስ ነው።
    እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ!