ሩህ ሚዲያ – Ruh Media

Find articulated views on the Fabrics of Ethiopian society & the world at large. There is no limit of topics of address: culture, lifestyle, history, art, literature, politics and economy. Habtamu Girma's page shares opinions, viewpoints, and/or commentaries on issues that matters for us all!!!

ሩህ ሚዲያ የተለያዩ የዲጂታል የብዝሃ-መገናኛ አማራጮችን በመጠቀም በአፍሪካ፣ በተለይ በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ አስተዳደርና ፖሊሲ፣ ፖለቲካል ኢኮኖሚ፣ ጂኦ-ኢኮኖሚክስ፣ ጂኦ-ፖለቲካ ጉዳዮች ዙሪያ በእውቀትና በዕውነት የተቀረጹ መረጃዎችን ለህዝብ ማድረስን ዓላማው ያደረገ ሚዲያ ነው፤ ዓላማውም በአገራዊ ኢኮኖሚያዊ አጀንዳዎች ላይ የሚኖረን ግንዛቤ በጥናትና በዕውቀት የተደገፈ እንዲሆን ጥረት ማድረግ ነው፤ በሩህ ሚዲያ ውስብስብ የሆኑ የኢኮኖሚ ጽንሰ ሃሳቦች እና የፖሊሲ እርምጃዎችን በቀላሉ ህዝብ በሚረዳው መንገድ ለማቅረብ ጥረት ይደረጋል // Ruh Media is aimed at addressing contextual factors associated to African economy, politics, geo-economics, natural resource conservation & management, climate change and energy transition issues. Ruh Media produces original contents capturing the human stories behind statistics, and showing how continental (African) and Ethiopian specific developmental aspirations translate into community-level change // የሩህ ሚዲያ ድህረ ገጽና የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይጎብኙ፤ ይወዳጁ!

ግንቦት 20 የሚዘከረው ቀኑ የህዝባችን ቁስል የተሻረበት የምሥራች ቀን እስከሆነ ጊዜ ድረስ ነው!

ማስታወሻ፦ ይህ መጣጥፍ ግንቦት 19 ቀን 2011 ዓ.ም የተጻፈ ነው፤ በድጋሚ የለጠፍሁት የያዘው ሃሳብ ዛሬም ጉዳይ ሆኖ ያለ በመሆኑ ነው።



በዘመናዊ የኢትዮጵያ ታሪክ በተለያየ ዘመን የተፈራረቁ አገዛዞች ሥልጣን የጨበጡት በሃይል እንደሆነ ሀቅ ነው። እናም የስልጣን በትር በእጃቸው ያስገቡበትን ቀን የድል ቀን አድርገው ደንግገዋል። ግርማዊነታቸው ጥቅምት 23 ቀን፣ ደርግ መስከረም 2 ቀን፣ ኢህአዴግ ግንቦት 20 ቀንን ብሔራዊ በዓል ብለው አውጀዋል።

በዘመን ዥረት አንዱ ሥርዓት በሌላው እየተተካ ቢመጣም ቴዲ አፍሮ እንደተቀኘው ለህዝቡ አዲስ ንጉስ እንጂ ለውጥ ከቶም አልመጣለትም ነበር።

የሥርዓት ለውጥ ሲመጣ የተሻለ ነገን የተመኘ ሁሉ ቀናቱ የሆነ የምስራች ይዘው ይመጡ ዘንድ እየተመኘ ሲዘክር ቆይቷል፥ በጊዜ ሂደት ግን አገዛዞቹ ከቀደመው ብሰው ሲገኙ ቀናቱን ከማወደስ ይልቅ ሲረግም ኖሯል።

እርግማኑም ‘ሰምሮለት’ የቀደመው የድል ቀን ተሽሮ በሌላ የድል ቀን ሲተካ ኖሯል።

በእኔ ምልከታ ግንቦት 20 ን ስናከብር አንድ በሰላማዊ መንገድ ለመስተካከል ያልቻለ ሥርዓት በሚገባው(ላልቶ ይነበብ) መንገድ የተቀየረበት ቀን እንጂ በራሱ ግብ ሆኖ መታየት አልነበረበትም።

ግንቦት 20 ለኢትዮጵያ ህዝብ ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ እውን ትሆን ዘንድ የብስራት ቀን ተስፋ ነበር እንጂ ዲሞክራሲና ፍትህ ያሰፈነ ለመሆኑ ምስክር ጊዜ፣ እማኙ ህዝብ ነው።

የግንቦት 20 አከባበር እንድምታ ግን ከዚህ በተቃራኒ ነበር። የኢህአዴግ ዲስኩር በዝቶ፣በጉራ ብቻ ተሞልቶ፤ ታገልኩለት ለሚለው ዓላማ ረገድ ራሱ ጠላት መሆኑ በጊዜ ሂደት ተረጋገጠ።

ኢህአዴጎች ለለውጥ የተሰዉ ውድ ጓዶቻቸው አጥንት ሳይወቅሳቸው እንዳሻቸው ሲፈነጩ ከርመው እነርሱም ከህዝብ ማዕበል ሳያመልጡ ይኸው የቀደምቶቻቸው እጣ ደርሷቸው ግንቦት 20 የጮቤ ቀን መሆኑ እንዳከተመ ጊዜ ምስክር ሆኖ፣ እኛም እማኝ ሆነናል።

የዶ/ር አብይ አስተዳደር በይፋ ባያውጅም ግንቦት 20 ን በመጋቢት 24 ለመተካቱ ብዙ አስረጅዎችን ማቅረብ ይቻላል።

መራራ ኑሮ እስከቀጠለ ድረስ ህዝቡ ለለውጥ መስዋዕት መሆኑ የህይወት እውነት ነው። ህዝብ ሌላ የተስፋ ቀን፣ ሌላ የምስራች ቀን ሽቶ ሲባዝን የመኖሩ ጉዳይም ሌላ የህይወት እውነት ሆኖ ይቀጥላል።

አሁንም የለውጥ ሀይል ነን ብለው ለህዝብ ተስፋ የሰጡና ሥልጣን የተቆናጠጡት ለተነሱለት ዓላማ ካልታመኑ፣ ከቀደመው መማር ካልቻሉ፣ ለውጥ ያወጁበት መጋቢት 24 ቀን የተስፋ ሳይሆን የመርገምት ቀን ተብሎ በህዝብ መፈረጁ አይቀሬ ነው።

ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን አብዝቶ ይባርክ! አሜን!!!



Discover more from ሩህ ሚዲያ – Ruh Media

Subscribe to get the latest posts sent to your email.

Posted in

አስተያየት ያስቀምጡ

ይህ ጣቢያ አይፈለጌ መልዕክትን ለመቀነስ Akismet ይጠቀማል። የአስተያየትዎ ውሂብ እንዴት እንደሚሰናዳ ይወቁ

Discover more from ሩህ ሚዲያ - Ruh Media

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading