ክብር እና ሞገስ ለዓድዋ ለሰማዕታት!
ሀብታሙ ግርማ
የካቲት 23 ቀን 2012 ዓ.ም
ጅግጅጋ፣ኢትዮጵያ
ዳግማዊ አጤ ምኒልክ፣ ንጉሰ ነገስት ዘ ኢትዮጵያ፤ የካቲት 23 1888 ዓ.ም ለኢትዮጵያዊያን ያሰሙት የድል ብስራት ይህ ነበር፦
“….የምስራች! በእግዚአብሄር ቸርነት የየካቲት ቅዱስ ጊዮርጊስ ዕለት ጣሊያንን ድል አድርጌ መታሁት። በጨረቃ ሲገሰግስ አድሮ እሰፈሬ ድረስ መጥቶ ገጠመኝ። አምላክ ኃያላን ረድቶኝ ፈጀሁት፤ ደስ ብሎኛል ደስ ይበልህ”
አባቶቻችን ከ124 ዓመታት በፊት የኢጣሊያ ወራሪ ሀይልን ድል የነሱት ከራሳቸው በፊት አገር አስቀድመው መስዋዕት መሆን መርሃቸው ስለነበር ነው።
የወቅቱ የሀገሬ ትውልድ መርሁ ከራስ በላይ ንፋስ ሆኖ የበዛ ራስ ወዳድነት የአገር አንድነት እና ሉዓላዊነትን ለአደጋ ያጋለጠ የዘመናችን ጠላት ሆኗል፤ ዛሬ የራሳችን ጠላት ራሳችን ሆነናል!
በመሆኑም የአድዋ ድልን ስንዘክር፦
*ራሳችንን ለማሸነፍ ቃል የምንገባበት፣
*ነገ የዛሬ መስዋዕትነት ውጤት መሆኑን የምንገነዘብበት፣ *ምክንያታዊነትን ገዢ መርህ የምናደርግበት፣
እንዲሆን እመኛለሁ!
ክብር እና ሞገስ ለሰማዕታት!

አስተያየት ያስቀምጡ