ሩህ ሚዲያ – Ruh Media

Find articulated views on the Fabrics of Ethiopian society & the world at large. There is no limit of topics of address: culture, lifestyle, history, art, literature, politics and economy. Habtamu Girma's page shares opinions, viewpoints, and/or commentaries on issues that matters for us all!!!

ሩህ ሚዲያ የተለያዩ የዲጂታል የብዝሃ-መገናኛ አማራጮችን በመጠቀም በአፍሪካ፣ በተለይ በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ አስተዳደርና ፖሊሲ፣ ፖለቲካል ኢኮኖሚ፣ ጂኦ-ኢኮኖሚክስ፣ ጂኦ-ፖለቲካ ጉዳዮች ዙሪያ በእውቀትና በዕውነት የተቀረጹ መረጃዎችን ለህዝብ ማድረስን ዓላማው ያደረገ ሚዲያ ነው፤ ዓላማውም በአገራዊ ኢኮኖሚያዊ አጀንዳዎች ላይ የሚኖረን ግንዛቤ በጥናትና በዕውቀት የተደገፈ እንዲሆን ጥረት ማድረግ ነው፤ በሩህ ሚዲያ ውስብስብ የሆኑ የኢኮኖሚ ጽንሰ ሃሳቦች እና የፖሊሲ እርምጃዎችን በቀላሉ ህዝብ በሚረዳው መንገድ ለማቅረብ ጥረት ይደረጋል // Ruh Media is aimed at addressing contextual factors associated to African economy, politics, geo-economics, natural resource conservation & management, climate change and energy transition issues. Ruh Media produces original contents capturing the human stories behind statistics, and showing how continental (African) and Ethiopian specific developmental aspirations translate into community-level change // የሩህ ሚዲያ ድህረ ገጽና የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይጎብኙ፤ ይወዳጁ!

ዛሬ ኢትዮጵያ  የውጭ ጠላት የላትም፤ የውስጥ እንጂ!

ክብር እና ሞገስ ለዓድዋ ለሰማዕታት!


ሀብታሙ ግርማ
የካቲት 23 ቀን 2012 ዓ.ም
ጅግጅጋ፣ኢትዮጵያ


ዳግማዊ አጤ ምኒልክ፣ ንጉሰ ነገስት ዘ ኢትዮጵያ፤ የካቲት 23 1888 ዓ.ም ለኢትዮጵያዊያን ያሰሙት የድል ብስራት ይህ ነበር፦
“….የምስራች! በእግዚአብሄር ቸርነት የየካቲት ቅዱስ ጊዮርጊስ ዕለት ጣሊያንን ድል አድርጌ መታሁት። በጨረቃ ሲገሰግስ አድሮ እሰፈሬ ድረስ መጥቶ ገጠመኝ። አምላክ ኃያላን ረድቶኝ ፈጀሁት፤ ደስ ብሎኛል ደስ ይበልህ”


አባቶቻችን ከ124 ዓመታት በፊት የኢጣሊያ ወራሪ ሀይልን ድል የነሱት ከራሳቸው በፊት አገር አስቀድመው መስዋዕት መሆን መርሃቸው ስለነበር ነው።

የወቅቱ የሀገሬ ትውልድ መርሁ ከራስ በላይ ንፋስ ሆኖ የበዛ ራስ ወዳድነት የአገር አንድነት እና ሉዓላዊነትን ለአደጋ ያጋለጠ የዘመናችን ጠላት ሆኗል፤ ዛሬ የራሳችን ጠላት ራሳችን ሆነናል!

በመሆኑም የአድዋ ድልን ስንዘክር፦
*ራሳችንን ለማሸነፍ ቃል የምንገባበት፣
*ነገ የዛሬ መስዋዕትነት ውጤት መሆኑን የምንገነዘብበት፣ *ምክንያታዊነትን ገዢ መርህ የምናደርግበት፣

እንዲሆን እመኛለሁ!

ክብር እና ሞገስ ለሰማዕታት!


Discover more from ሩህ ሚዲያ – Ruh Media

Subscribe to get the latest posts sent to your email.

Posted in

አስተያየት ያስቀምጡ

ይህ ጣቢያ አይፈለጌ መልዕክትን ለመቀነስ Akismet ይጠቀማል። የአስተያየትዎ ውሂብ እንዴት እንደሚሰናዳ ይወቁ

Discover more from ሩህ ሚዲያ - Ruh Media

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading