ሀብታሙ ግርማ
ጥር 19 ቀን 2012 ዓ.ም
ጅግጅጋ፣ኢትዮጵያ
የጽሑፌ መነሻ አቶ ልደቱ በአብይ አህመድ የአመራር ብቃት ላይ በአስራት (ASRAT) ቴሌቭዥን የሰጠው አስተያየት ነው (ከታች ምስሉን ይመልቱ)። በእኔ አተያይ አስተያየቱ በራሱ ቅንነት የጎደለው ነው። ምክንያቱም አቶ ልደቱ በኢትዮጵያ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ እያወቀ እንደማያውቅ ሆኖ የተናገረው ነው።

መሪያችን በስንት ገመድ እየተጎተተ እንዳለ እንኳን እንደ አቶ ልደቱ አያሌው ያለ አንጋፋ ፖለቲከኛ ለማንኞውም ዜጋ የተሰወረ ሀቅ አይደለም።
ብሔርተኞች በየፈርጃቸው ፍላጎታቸውን እንዲያስፈጽምላቸው ሲውተረተሩ፣ ህወሓት በውስጠ ፓርቲ ቅራኔ ፌዴራል ሥርዓቱን ለማዳከም ቀን ከሌት እየሰራ ባለበት ሁኔታ ይህ ሰው ብቻውን በብልሃት እና በጥበብ ፈተናዎቹን በአግባቡ እያለፈ ያለ መሪ ነው።
አብይ ከብዙ አቅጣጫ እየተጋፈጠ ያለው የገመድ ጉተታ እልባት የሚያገኘው፣ በዚህም ከተለያዩ ዋልታ ረገጥ ፖለቲካዊ ፍላጎቶች ተጽዕኖ ተላቅቆ የሚያስወቅስም ሆነ የሚያስመሰግን ውሳኔ ሊወስን የሚችለው ከምርጫው በኋላ ነው።
በእኔ እምነት በዚህ ሰዓት እንደ አብይ አህመድ የብዙሃንን ፍላጎት አስማምቶ የመምራት ብቃትም፣ ጽናት እና ቅቡልነት ያለው መሪ የለም። ይህን ስል ግን አብይ ከፈጣሪ የተላከ መልአክ፣ ተኪ የሌለው መሪ ነው ማለቴ አይደለም።
አብይ አህመድን እንደ መንግስት ለመውቀስ ተገቢ የሚሆነው ከምርጫው በኋላ ነው። ያኔ ጠቅላዩ ሙሉ ስልጣኑን ወይ ያሸንፋል ወይም አሁን በወቀሳ የተጠመድን ዜጎችም ሆነ ፖለቲከኞች መንግስት ለሚመሰርተው አካል በህግ የመገዛት ግዴታ የሚኖርብን ይሆናል። ለሁሉም የሚወስነው ጊዜና ጊዜ ብቻ ነው። እድሜ ይስጠንና ሁሉንም እናያለን።
ነገር ግን የነገ እጣ ፈንታችንን የሚወስነው የዛሬ ውሳኔያችን ነውና የማንዐጸትበት ውሳኔ እንድንሰጥ ይገባል። የማንጸጸትበት ውሳኔ ማለት ውሳኔያችን የሚያስከትለውን በጎም ሆነ አሉታዊ ገጽ ለመቀበል መዘጋጀት ማለት ነው። አንዴ ከወሰንን በኋላ ይህ በሆነ ኖሮ፣ ኖሮ፣ ኖሮ አይሰራም።

አስተያየት ያስቀምጡ