ሩህ ሚዲያ – Ruh Media

Find articulated views on the Fabrics of Ethiopian society & the world at large. There is no limit of topics of address: culture, lifestyle, history, art, literature, politics and economy. Habtamu Girma's page shares opinions, viewpoints, and/or commentaries on issues that matters for us all!!!

ሩህ ሚዲያ የተለያዩ የዲጂታል የብዝሃ-መገናኛ አማራጮችን በመጠቀም በአፍሪካ፣ በተለይ በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ አስተዳደርና ፖሊሲ፣ ፖለቲካል ኢኮኖሚ፣ ጂኦ-ኢኮኖሚክስ፣ ጂኦ-ፖለቲካ ጉዳዮች ዙሪያ በእውቀትና በዕውነት የተቀረጹ መረጃዎችን ለህዝብ ማድረስን ዓላማው ያደረገ ሚዲያ ነው፤ ዓላማውም በአገራዊ ኢኮኖሚያዊ አጀንዳዎች ላይ የሚኖረን ግንዛቤ በጥናትና በዕውቀት የተደገፈ እንዲሆን ጥረት ማድረግ ነው፤ በሩህ ሚዲያ ውስብስብ የሆኑ የኢኮኖሚ ጽንሰ ሃሳቦች እና የፖሊሲ እርምጃዎችን በቀላሉ ህዝብ በሚረዳው መንገድ ለማቅረብ ጥረት ይደረጋል // Ruh Media is aimed at addressing contextual factors associated to African economy, politics, geo-economics, natural resource conservation & management, climate change and energy transition issues. Ruh Media produces original contents capturing the human stories behind statistics, and showing how continental (African) and Ethiopian specific developmental aspirations translate into community-level change // የሩህ ሚዲያ ድህረ ገጽና የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይጎብኙ፤ ይወዳጁ!

ኢትዮጵያን ያቀፍናት መስሎን እንዳናንቃት!

ሀብታሙ ግርማ ደምሴ (በጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ ረዳት ፕሮፌሰር)
ጥር 12 ቀን 2012 ዓ.ም

የጽሑፌን ርዕስ ተዋስኩት በአንድ ወቅት ጋዜጠኛ ታምራት ነገራ አክራሪ የኢትዮጵያ ብሔርተኝነትን ለመንቀፍ የተጠቀመበት ሀረግ ነው፡፡ የዚህ ጽሑፍ ዓላማም አክራሪ ኢትዮጵያዊ ብሔርተኝነትን መንቀፍ ነው፡፡

ብሔርተኝነት ክፋት የለውም፤ አክራሪ ብሔርተኝነት ሲሆን ነው ችግሩ፡፡ አክራሪነት ጠንቁ ለራሱ ላከረረው ወገን ወይም ቡድን ነው፡፡ በኢትዮጵያ የአሁናዊ ገጽታዎች ዋነኛው አክራሪነት ነው፤ በብሔር አልያም በኢትዮጵያዊነት ጥላ ስር ቆመናል ብለው የፖለቲካ አጀንዳቸው ያደረጉ ሐይሎች በአክራሪነት ቀውስ ውስጥ ራሳቸውን ዘፍቀው፤ ራሳቸው ተቸግረው አገር እና ህዝብን እያስቸገሩ ነው፡፡

በሰሞኑ የጥምቀት በዓል ላይ ከተስተዋሉ ነገሮች አንዱ የባንዲራ ውዝግብ ጉዳይ ነው፡፡ እኔ እስከማውቀው ድረስ በስፋት ህዝብ ይዞት የሚወጣው ልሙጡ አረንጋዴ፣ ቢጫ፣ ቀይ አርማም ሆነ ባንዲራ አይደለም ፤ ህጋዊ እውቅናም የለውም፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አርማም ይህ ባንዲራ አይደለም፡፡ የቤተክርስቲያኒቱ ይፋዊ መለያ አረንጋዴ፣ ቢጫ፣ቀይ ሆኖ በመሃል አርማ ያለው ነው (ምስሉን ይመልከቱ)፡፡

በኢትዮጵያ የታሪክ ትርክት ሆነ የፖለቲካ አሰላለፎች እንደምናየው ልሙጡ ባንዲራ ያለፈው የጭቆና ስርዓት ምልክት እንደሆነ የሚያነሱ የብሔር ሆነ የሃይማኖት ማህበረሰብ ክፍሎች አሉ፡፡ ለአብዛኞቹ ብሔሮች እና ብሔረሰቦች ይህን ባንዲራ ማውለብለብ ትርጉሙ ያለፈው ብሔራዊ ጭቆናን ማወደስ ነው፤ በለብዙሃኑ የእስልምና እንዲሁም የፕሮቴስታንት ክርስትና ተከታይ ኢትዮጵያዊንም ትርጉሙ እንዲሁ ነው፡፡

ኢትዮጵያ፤ ኢትዮጵያ የምንል ወገኖች የምር ኢትዮጵያን የምንፈልጋት ከሆነ በሌሎች ወንድሞቻችንን ቁስል ላይ ሌላ ህመም ባንጨምር ጥሩ ነው፡፡ ለኢትዮጵያ ቀናዒ ከሆንን ብዝሃነትን ማክበር አለብን፡፡ ይህ ካልሆነ ግን የፉክክር ቤት ሳይዘጋ ያድራል እንዲሉ የምንጮኽላት ኢትዮጵያ ህልም ሆና ትቀራለች፤ ኢትዮጵያ ህልም ከሆነች ራዕያችን ሁሉ ህልም ሆኖ ይቀራል፡፡

አባቶች በደም እና በአጥንት ያስረከቡንን ውድ አገር እኛ ደግሞ በጭብጨባ እያፈረስን ለን አሳፋሪ ትውልዶች መሆናችን ያሳዝናል፡፡

ለአፍታም ቢሆን በአገር አልባነት ውስጥ የእያንዳንዳችን ህይወት ምን እንደሚመስል እናስብ፤ በፈረሰ አገር ውስጥ፡-
ስራ የለም! ቤተሰብ የለም! ልጅ ወልዶ መሳም የለም! መንፈሳዊ ህይወት የለም! ቤተ ክርስቲያን፣ መስጊድ የለም! ሳቅና ጨዋታ የለም! ደመወዝ የለም! ቢራ የለም! ጫት መቃም የለም! መስከርም ሆነ መመርቀን የለም! ጮማ መቁረጥ የለም! ወጥቶ መግባት የለም! ምንም የለም


Discover more from ሩህ ሚዲያ – Ruh Media

Subscribe to get the latest posts sent to your email.

Posted in

አስተያየት ያስቀምጡ

ይህ ጣቢያ አይፈለጌ መልዕክትን ለመቀነስ Akismet ይጠቀማል። የአስተያየትዎ ውሂብ እንዴት እንደሚሰናዳ ይወቁ

Discover more from ሩህ ሚዲያ - Ruh Media

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading