ሩህ ሚዲያ – Ruh Media

Find articulated views on the Fabrics of Ethiopian society & the world at large. There is no limit of topics of address: culture, lifestyle, history, art, literature, politics and economy. Habtamu Girma's page shares opinions, viewpoints, and/or commentaries on issues that matters for us all!!!

ሩህ ሚዲያ የተለያዩ የዲጂታል የብዝሃ-መገናኛ አማራጮችን በመጠቀም በአፍሪካ፣ በተለይ በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ አስተዳደርና ፖሊሲ፣ ፖለቲካል ኢኮኖሚ፣ ጂኦ-ኢኮኖሚክስ፣ ጂኦ-ፖለቲካ ጉዳዮች ዙሪያ በእውቀትና በዕውነት የተቀረጹ መረጃዎችን ለህዝብ ማድረስን ዓላማው ያደረገ ሚዲያ ነው፤ ዓላማውም በአገራዊ ኢኮኖሚያዊ አጀንዳዎች ላይ የሚኖረን ግንዛቤ በጥናትና በዕውቀት የተደገፈ እንዲሆን ጥረት ማድረግ ነው፤ በሩህ ሚዲያ ውስብስብ የሆኑ የኢኮኖሚ ጽንሰ ሃሳቦች እና የፖሊሲ እርምጃዎችን በቀላሉ ህዝብ በሚረዳው መንገድ ለማቅረብ ጥረት ይደረጋል // Ruh Media is aimed at addressing contextual factors associated to African economy, politics, geo-economics, natural resource conservation & management, climate change and energy transition issues. Ruh Media produces original contents capturing the human stories behind statistics, and showing how continental (African) and Ethiopian specific developmental aspirations translate into community-level change // የሩህ ሚዲያ ድህረ ገጽና የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይጎብኙ፤ ይወዳጁ!

እየተንሰራፋ የመጣው የኩላሊት ህመም ከጤና ባሻገር የፖለቲካል-ኢኮኖሚ ገጽታ ይኖረው ይሆን?

ሀብታሙ ግርማ
ጥር 5 ቀን 2012 ዓ.ም
ጅግጅጋ፣ ኢትዮጵያ



በኢትዮጵያ የጊዜው አሳሳቢ የጤና እክል የኩላሊት ስራውን የማቆም በሽታ (End-Stage Renal Disease (ESRD) ነው። በሽታው በአብዛኛው በከተማው የኢትዮጵያ ማህበረሰብ፣ በተለይም አምራች የሰው ሀይል ክፍልን በስፋት እያጠቃ ይገኛል።

አንባቢያን የህመሙ ምክንያቶች፣ ምልክቶች፣ የህክምና አማራጮች፣ እና የጥንቃቄ ምክር ከሚከተለው ሊንክ ሊያገኙ ይችላሉ፦ https://www.kidneyfund.org/kidney-disease/kidney-failure/

የጤና ባለሙያ ስላልሆንኩ ስለጉዳዩ ትንተና መስጠት አልችልም። ነገር ግን በአጭር ጊዜ በሽታው አጣዳፊ የማህበረሰብ ጤና እክል ደረጃ የመድረሱ ነገር ከጤና ባለፈ የፖለቲካል-ኢኮኖሚ ገጽታ ይኖረው ይሆን የሚል ጥያቄን አጭሮብኛል።

በእርግጥም መንግስት እና ለመንግስት ቅርበት ያላቸው ነጋዴዎች ባለፉት አመታት በምግብ እና ምግብ ነክ ምርቶች እንዲሁም በመድሃኒት ንግድ ላይ በስፋት መሳተፋቸው በምርቶቹ ጥራት ቁጥጥር ላይ የራሱ አሉታዊ ተጽዕኖ እንደሚኖረው እገምታለሁ። ይህም ማህበረሰቡን እንደ ኩላሊት ያሉ ገዳይ በሽታዎች ተጋላጭ የሚሆንበትን ዕድል ማስፋቱ የማይቀር ነው።

ከዚህ አንጻር እነዚህ ከታች የማነሳቸው ነጥቦች ማየት
ያሻል፦

በሽታው እንዲህ በአጭር ጊዜ የመንሰራፋቱን ጉዳይ መንግስት ጉዳዩ በሚፈልገው ልክ ምላሽ ያለመስጠቱ ምክንያት ምን ይሆን?

ስለ በሽታው ማህበረሰባዊ ግንዛቤ ከማስጨበጥ ይልቅ ወ
ወይም ከመከላከል ይልቅ ለማከም የሚደረገው ሩጫ ጎልቶ የመታየቱ ነገር ቢፈተሽ፤ ከዚህ አንጻር የዲያሊሲስ ህክምና ውድነት ህክምናው እንደ ቢዝነስ እድል የመጠቀሙ ነገር አዝማሚያ ይኖራል።

መንግስት የአገር ድንበርን ለመጠበቅ ሰራዊት አሰልጥኖ እንደሚያሰማራው ሁሉ ዜጎቹን እንደ ኩላሊት ህመም አይነት ገዳይ በሽታዎች የመጠበቅ ግዴታ አለበት። ከዚህ አንጻር በሽታው በአመጋገብ ስርዓት እና/ወይም መሰረታዊ የምግብ ማዘጋጃዎች እንደ ዘይት፣ ቅመማ ቅመሞች፣ የምግብ ማሸጊያ እቃዎች፣ የምግብ እና ምግብ ነክ እቃዎች የምርት ጥራት፣ የአገልግሎት ዘመን ክትትል፣ የሚጓጓዙበት እና የሚከማቹበት ሁኔታ ተገቢው ክትትል እና ቁጥጥር መደረግ አለበት።


Discover more from ሩህ ሚዲያ – Ruh Media

Subscribe to get the latest posts sent to your email.

Posted in

አስተያየት ያስቀምጡ

ይህ ጣቢያ አይፈለጌ መልዕክትን ለመቀነስ Akismet ይጠቀማል። የአስተያየትዎ ውሂብ እንዴት እንደሚሰናዳ ይወቁ

Discover more from ሩህ ሚዲያ - Ruh Media

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading