• አብይ አህመድን መውቀስ ተገቢነቱ ከምርጫ በኋላ ነው!

    ሀብታሙ ግርማ
    ጥር 19 ቀን 2012 ዓ.ም
    ጅግጅጋ፣ኢትዮጵያ



    የጽሑፌ መነሻ አቶ ልደቱ በአብይ አህመድ የአመራር ብቃት ላይ በአስራት (ASRAT) ቴሌቭዥን የሰጠው አስተያየት ነው (ከታች ምስሉን ይመልቱ)። በእኔ አተያይ አስተያየቱ በራሱ ቅንነት የጎደለው ነው። ምክንያቱም አቶ ልደቱ በኢትዮጵያ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ እያወቀ እንደማያውቅ ሆኖ የተናገረው ነው።

    መሪያችን በስንት ገመድ እየተጎተተ እንዳለ እንኳን እንደ አቶ ልደቱ አያሌው ያለ አንጋፋ ፖለቲከኛ ለማንኞውም ዜጋ የተሰወረ ሀቅ አይደለም።

    ብሔርተኞች በየፈርጃቸው ፍላጎታቸውን እንዲያስፈጽምላቸው ሲውተረተሩ፣ ህወሓት በውስጠ ፓርቲ ቅራኔ ፌዴራል ሥርዓቱን ለማዳከም ቀን ከሌት እየሰራ ባለበት ሁኔታ ይህ ሰው ብቻውን በብልሃት እና በጥበብ ፈተናዎቹን በአግባቡ እያለፈ ያለ መሪ ነው።

    አብይ ከብዙ አቅጣጫ እየተጋፈጠ ያለው የገመድ ጉተታ እልባት የሚያገኘው፣ በዚህም ከተለያዩ ዋልታ ረገጥ ፖለቲካዊ ፍላጎቶች ተጽዕኖ ተላቅቆ የሚያስወቅስም ሆነ የሚያስመሰግን ውሳኔ ሊወስን የሚችለው ከምርጫው በኋላ ነው።

    በእኔ እምነት በዚህ ሰዓት እንደ አብይ አህመድ የብዙሃንን ፍላጎት አስማምቶ የመምራት ብቃትም፣ ጽናት እና ቅቡልነት ያለው መሪ የለም። ይህን ስል ግን አብይ ከፈጣሪ የተላከ መልአክ፣ ተኪ የሌለው መሪ ነው ማለቴ አይደለም።

    አብይ አህመድን እንደ መንግስት ለመውቀስ ተገቢ የሚሆነው ከምርጫው በኋላ ነው። ያኔ ጠቅላዩ ሙሉ ስልጣኑን ወይ ያሸንፋል ወይም አሁን በወቀሳ የተጠመድን ዜጎችም ሆነ ፖለቲከኞች መንግስት ለሚመሰርተው አካል በህግ የመገዛት ግዴታ የሚኖርብን ይሆናል። ለሁሉም የሚወስነው ጊዜና ጊዜ ብቻ ነው። እድሜ ይስጠንና ሁሉንም እናያለን።

    ነገር ግን የነገ እጣ ፈንታችንን የሚወስነው የዛሬ ውሳኔያችን ነውና የማንዐጸትበት ውሳኔ እንድንሰጥ ይገባል። የማንጸጸትበት ውሳኔ ማለት ውሳኔያችን የሚያስከትለውን በጎም ሆነ አሉታዊ ገጽ ለመቀበል መዘጋጀት ማለት ነው። አንዴ ከወሰንን በኋላ ይህ በሆነ ኖሮ፣ ኖሮ፣ ኖሮ አይሰራም።

  • THE CONCERN OF ABDUCTED GIRLS IS THE CONCERN OF HUMANITY!

    Habtamu Girma
    January 25, 2020
    Jigjiga, Ethiopia



    The concern of abducted female students in western Ethiopia should not be politicized. The issue should not be subjected to affiliations with abductees as a family, friend, neighbour, shared identities like sex, ethnicity, religion, citizenship or whatever.

    To condemn the infliction against these young and hopeful girls, the affiliation should be humanity.

    As a matter of fact, the infliction happened against these hopeful girls is a mind rape. Raping a mind is nothing but robbing one’s hope, and hence denying his/her future.

    In essence, there is no more cruelty than raping the mind of a humankind. Because, no one can stand while his/her mind raped. Hence, justifying the abduction of these young girls is inhumane.

    Above all, any failure to condemn such barbaric act amounts perpetrating with homiciders against virtues of humanity!

    Therefore,

    Let’s all shout for the release of abductees! Let’s all voice against the growing impunity in Ethiopia!

  • ፖለቲካችን እና ፖለቲከኞቻችን እኛው ራሳችንን ይመስላሉ !!!

    ሀብታሙ ግርማ (በጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ ረዳት ፕሮፌሰር)

    ዛሬ በውድ የኢትዮጵያ ወጣቶች ደም ስንናፍቀው የኖርነውን የነጻነት አየር መተንፈስ በጀመርንበት ወቅት የኢትዮጵያ ህዝብ እርስ በርስ ለመነቋቆር እና ለመበጣበጥ የሚነሳበት ምክንያት የለውም፤ ነገሩ የፖለቲካ አጀንዳ ልዩነት (ቢኖር እንኳ በንግግር መፍታት ይቻላል) ሳይሆን የአመል ነው። የአመል ችግር የሚለውን የሚጠቀልል የአማርኛ ቃል የቅንነት ችግር (Lack of integrity) ነው። የፖለቲካችን ስንክሳርም ይህ የቅንነት ችግር ነው፡፡

    ፖለቲካችን ከሽኩቻ፣ ከጥሎ ማለፍ እና ሴራ ያልተላቀቀው በምንም ሳይሆን በልሂቃኖቻችን ባህሪያዊ ምክንያቶች ነው፡፡ የዚህ ሁሉ መሰረቱ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣው አጥፊ ባህላችን የራሱ አስተዋጽኦ አለው፡፡ ይህም ልዩነቶችን በንግግር ሳይሆን ከሆነ በጠብ፣ በሴራ፣ ካልሆነ በኩርፊያ መፍታት ባህላችን መሆኑ ነው፡፡ ቅንነት የሌለበት የህይወት እንቅስቃሴ ሁሉ ጨው የሌለው ወጥ እንደማለት ነው፡፡ ኑራችንን ሁሉ አያጣፍጠውም፤ የአንዳችን ማሸነፍ የሌላችን መሸነፍ፤ የአንዱ መሻል የሌላው መቆርቆዝ፤ የአንዱ ማግኘት የሌላው ማጣት፤ የአንዳችን ማደግ የሌላው መደህየት ይመስለናል፡፡

    እናም ሁል ጊዜ ነገሮችን የምንረዳበት መነጽር ሁሉ ከነባራዊ ሁኔታዎች (ለምሳሌ ከጊዜ፣ ከቦታ፣ ከሁኔታ) አንጻር ሳይሆን ከራሳችን ፍላጎት አንጻር ነው፡፡ በዚህም ነገራችንን ስንመዝን ከራሳችን ድክመት ወይም ጥንካሬ አንጻር ሳይሆን በቅርባችን ካሉ፣ ከምናውቃቸው ሰዎች ነው፡፡ ኢትዮጵያዊያን በሌሎች ላይ መፍረድ ልማዳችን ነው፡፡

    ሀይማኖተኛ ህዝብ ነን ብንልም እምነት ላይ እምብዛም ነን፤ አትፍረድ ይፈረድብሃል፤ በልንጀራህን ከራስህ አስበልጠህ ውደድ፤ ሁለት ካለህ አንዱን አካፍል ወዘተ…. የሚሉት የአምላክ መመሪያዎች ጉዳችን አይደሉም፡፡

    ከሌሎች ጥንካሬ ለመውሰድ ከመሞከር ይልቅ የሌሎችን ስኬት የማሳነስ፣ የበታችነት ስሜት፣ እኔስ ከማን አንሼ የህይወት መመሪያዎቻችን ናቸው፡፡ ኑራችን ሁሉ ከራሳችን ጋር ሳይሆን በሌሎች ህይወት ውስጥ ነው፤ ለዚህም ነው በነገራችን ሁሉ መሻሻልን ለማምጣት የሚያስፈልገው የራስን ድክመትና ጥንካሬ ማወቅ ፍላጎቱም አቅሙም ያጣነነው፤ የዚህ ውጤት ወይም ነጸብራቅ ደግሞ በአብዛኛው የምናጠፋው ጊዜ ለራሳችን ህይወት መሻሻል በሚጠቅሙ ጉዳዮች ሳይሆን በረብ የለሽ ጉዳዮች ተጠምደን ነው፤ በማያልቅና አላስፈላጊ ፉክክር፣ በንትርክ አልያም ሽኩቻ መባዘናችን መገለጫችን ነው፡፡

    የፖለቲካ ልሂቃን የምንላቸው ከሌላ አገር ወይም ፕላኔት የመጡ ሳይሆኑ ከኛው ከህዝባችን የሚመዘዙ፣ የዚህ ጎጂ ባህላችን ሰለባዎች በመሆናቸው ከእያንዳንዳችን መደበኛ ዜጎች የተለየ ስብዕና እንዲኖራቸው መጠበቅ የዋህነት ነው፡፡ የፖለቲካችን ስሪት ወይም አይነተኛ መገለጫ ከላይ የተገለጸው፣ እርስ በርሳችን ያለን ግንኙነት መልክን ይመስላል፡፡

    ዋና ዋና የፖለቲካችን እና የፖለቲከኞቻችንን መገለጫዎች የኛኑ የእያንዳንዳችንን ስብዕናን ይመስላሉ፡፡

    የፖለቲካ አጀንዳዎቻችን ህዝባዊ ፋይዳ የሌለው መሆኑ፣ አንድ አይነት የፖለቲካ እሳቤ ይዞ ነገር ግን በተቃራኒው ጽንፍ የረገጠ የፖለቲካ ልዩነት አይነት ምስቅልቅል ፖለቲካ፤ የልሂቁ ክፍል የብስለት ደረጃ ፖለቲካ አጀንዳ ከሚፈልገው እና/ወይም ከሚጠበቀው በጣም የወረደ. መሆኑ፣ የፖለቲከኞቻችን ስብዕና ከመደበኛው ኢትዮጵያዊ ስብዕና ያልተሻለ መሆኑም ለዚያ ነው፡፡
    እዚህ ጋር ልብ ሊባል የሚገባው ትውልድ አሻጋሪ ሃሳብ አንግው ፖለቲካን የሚያራምዱ፣ በፖለቲካ ስብዕናቸውም ሆነ በግል ስብዕናቸው የላቁ ፖለቲከኞች ቢኖሩንም ቁጥራቸው እጅግ ጥቂት ነው፡፡

    በአጠቃላይ ቅን አለመሆናችን ለብዙ መከራ ዳርጎናል፤ ከቤተሰብ ጀምሮ እስከ አገራዊ ችግሮቻችን መነሾ ናቸው የምላቸው ምክንያቶች የዚሁ ውጤት ናቸው፤ የቅንነት ችግር ምልክቶች የሚከተሉት ናቸው፦
    • እውነትን ከሐሰት፤ ትክክለኛውን ከስህተተኛ ለመለየት የመንፈስ፣ የሞራልም ሆነ የአእምሮ ዝግጁነት ማጣት፣
    • በስሌት ሳይሆን በስሜት መነዳት፣
    • ለበረታው ዕውቅና ከመስጠትና በመንፈሳዊ ቅናት( rational selfishnes) ተነሳስተን ከስኬቱ ሂደት ለመማር ከመሞከር ይልቅ ስኬቱን ለማሳነስ መሞከር፣
    • ብልጣብልጥነት፣ ጮሌነት እና የድል አጥቢያ አርበኝነት።
    እኛ ኢትዮጵያውያን ቅን ብንሆን ኖሮ፦
    • በህይወት መስመራችን ጉዳያችን የሆነን ነገር የምናውቅ፣ በመሆኑም አላስፈላጊና ጥቃቅን የሆኑ ነገሮችን እንደ ጉዳይ ወስደን ራስ በራሳችንን ባላደከምን፣ የምናደርገው ነገር ሁሉ በምክንያት በሆነ፣ የድርጊቶቻችን ውጤት አንዱን ይዞ አንዱን መጣል አይነት ሆኖብን ለመንግስት ብቻ ሳይሆን ለፈጣሪ እንኳ አስቸጋሪ ህዝቦች ባልሆን ነበር።
    • ለተንሸዋረረ የታሪክ አረዳዳድ ባልተጋለጥን ነበር፤ የረጅም ዘመን ታሪካችን ለአንድነታችን መሠረት የሆኑ እጅግ በርካታ በጎ ሁነቶችን ያዘለ ቢሆንም ይህ የታሪክ እውነት ደብዝዞ በአንጻሩ ያለፈው በጎ ያልሆነው የታሪካችን አካል ባልደመቀ ነበር።
    • በታሪክ ሂደት ያሳለፍነው በርካታ መልካም እንደነበር ሁሉ መልካም ያልሆኑ ግንኙነቶች እንዳሳለፍን እንረዳ ነበር። በመሆኑም የምንወዳት እና የጋራ ቤታችን የሆነችው ኢትዮጵያ የምንላት አገር ህዝቦቿ በተለያዩ ምክንያቶች(ኃይማኖታዊ፣ የማንነት፣ ራስን በራስ የማስተዳዳር ወዘተ….) በተለያዩ ወቅቶች በአገራዊ እና አለማቀፋዊ ገፊ ምክንያቶች እርስ በርስ የተዋጉ፣ አንዱ ሌላውን ያስገበረበት ሁነቶች በርካታ መሆናቸውን በአንድ በኩል የመካድ በሌላው በኩል የማጉላት አዝማሚያ የፖለቲካችን መዘውር (pillar) ሆኖ ባልተቸገርን ነበር።
    • ዛሬ ላይ በጎ ያልሆነውን የታሪካችን አካል እና(ወይም) ወካይ ምልክቶቹን ማንሳታችን ተገቢነቱ ካለፈው ስህተታችን ለመማር እንጂ ለመነታረክ ፣ ለመበሻሸቅ፣ የአሸናፊነት ወይም የተሸናፊነት መንፈስ በማስረጽ ባልከፋፈለን ነበር።
    • በመሆኑም ዛሬ ላይ ይህን በጎ ያልሆነ የታሪክ አሻራ ጠባሳ ሰለባ ያልሆነ የኢትዮጵያ ህዝብ አካል የሆነ ብሔር፣ የሐይማኖት እና የፖለቲካ ቡድን አለመኖሩ፣ በዚህም የኢትዮጵያ ህዝብ የእነዚህ የማህበረብ ክፍሎች(ህዝቦች) ድምር መሆኑን ተረድተን፣ የመጥፎ ታሪካችን ሰለባ የነበሩትን ወገኖቻችንን የሚያበሳጩ፣ ሰቆቃቸውን የሚያስታውሱ ምልክቶች ለሌላኞቻችን የድል አድራጊነት፣ የአሸናፊነት፣ ምልክት ከማድረግ በተቆጠብን ነበር።
    • በአጠቃላይ ታሪካችን የመማሪያ ሳይሆን መጥፎ የታሪክ አሻራችን አገርሽቶ ሌላ መጥፎ ታሪክ ለመጭው ትውልድ ለሚያወርሱ እኩይ ድርጊቶች የሚጋብዝ፣ ትልቅ የተስፋ ጮራ የፈነጠቀውን የለውጥ ሂደት የሚቀለብስ፣ ሲከፋም የጋራ ቤታችን የምንላትን ኢትዮጵያ ምኞት ብቻ እንዳትሆን ትልቅ ስጋት ባልሆነ ነበር ።

    እኛ ኢትዮጵያዊን ቅንነት ቢኖረን ኖሮ፦
    • የአገር አንድነት እና የሉዓላዊነት ጉዳይ ጨምሮ በእለት ተዕለት ግንኙነቶቻችንን የምንወያየው እና የምንከራከረው ፋይዳ ስላለው ጉዳይ ይሆን፣ በእንቅሰቃሴዎቻችን ሁሉ ትልቁን ምስል ባልተጋረደብን ነበር፣
    • በታሪካችን አይተን የማናውቃቸው እንደ ለማ መገርሳ፣ ገዱ አንዳርጋቸው፣ አብይ አህመድ፣ ደመቀ መኮንን አይነት ጥሩ መሪዎች አግኝተን በነቢብ እየደገፍናቸው በገቢር ግን እየወጋናቸው መሆኑን መገንዘብ ይቻለን ነበር፤መልካም አመራራቸውን ለመደገፍ ከመጣር ይልቅ በየዕለቱ የቤት ስራ ባልሆንባቸው ነበር።

    ኢትዮጵያዊያን የቅንንነትን እሴቶችን እሴቶቻቸው በማድረግ ራሳቸውንም ሆና አገራቸውን ከጥፋት ይታደጉ ዘንድ ብቸኛው አማራጫቸው ነው።

    መጪው ጊዜ ሁላችንም ቅንነትን የምንለማመድበት ዘመን ይሆን ዘንድ እመኛለሁ።

  • ኢትዮጵያን ያቀፍናት መስሎን እንዳናንቃት!

    ሀብታሙ ግርማ ደምሴ (በጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ ረዳት ፕሮፌሰር)
    ጥር 12 ቀን 2012 ዓ.ም

    የጽሑፌን ርዕስ ተዋስኩት በአንድ ወቅት ጋዜጠኛ ታምራት ነገራ አክራሪ የኢትዮጵያ ብሔርተኝነትን ለመንቀፍ የተጠቀመበት ሀረግ ነው፡፡ የዚህ ጽሑፍ ዓላማም አክራሪ ኢትዮጵያዊ ብሔርተኝነትን መንቀፍ ነው፡፡

    ብሔርተኝነት ክፋት የለውም፤ አክራሪ ብሔርተኝነት ሲሆን ነው ችግሩ፡፡ አክራሪነት ጠንቁ ለራሱ ላከረረው ወገን ወይም ቡድን ነው፡፡ በኢትዮጵያ የአሁናዊ ገጽታዎች ዋነኛው አክራሪነት ነው፤ በብሔር አልያም በኢትዮጵያዊነት ጥላ ስር ቆመናል ብለው የፖለቲካ አጀንዳቸው ያደረጉ ሐይሎች በአክራሪነት ቀውስ ውስጥ ራሳቸውን ዘፍቀው፤ ራሳቸው ተቸግረው አገር እና ህዝብን እያስቸገሩ ነው፡፡

    በሰሞኑ የጥምቀት በዓል ላይ ከተስተዋሉ ነገሮች አንዱ የባንዲራ ውዝግብ ጉዳይ ነው፡፡ እኔ እስከማውቀው ድረስ በስፋት ህዝብ ይዞት የሚወጣው ልሙጡ አረንጋዴ፣ ቢጫ፣ ቀይ አርማም ሆነ ባንዲራ አይደለም ፤ ህጋዊ እውቅናም የለውም፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አርማም ይህ ባንዲራ አይደለም፡፡ የቤተክርስቲያኒቱ ይፋዊ መለያ አረንጋዴ፣ ቢጫ፣ቀይ ሆኖ በመሃል አርማ ያለው ነው (ምስሉን ይመልከቱ)፡፡

    በኢትዮጵያ የታሪክ ትርክት ሆነ የፖለቲካ አሰላለፎች እንደምናየው ልሙጡ ባንዲራ ያለፈው የጭቆና ስርዓት ምልክት እንደሆነ የሚያነሱ የብሔር ሆነ የሃይማኖት ማህበረሰብ ክፍሎች አሉ፡፡ ለአብዛኞቹ ብሔሮች እና ብሔረሰቦች ይህን ባንዲራ ማውለብለብ ትርጉሙ ያለፈው ብሔራዊ ጭቆናን ማወደስ ነው፤ በለብዙሃኑ የእስልምና እንዲሁም የፕሮቴስታንት ክርስትና ተከታይ ኢትዮጵያዊንም ትርጉሙ እንዲሁ ነው፡፡

    ኢትዮጵያ፤ ኢትዮጵያ የምንል ወገኖች የምር ኢትዮጵያን የምንፈልጋት ከሆነ በሌሎች ወንድሞቻችንን ቁስል ላይ ሌላ ህመም ባንጨምር ጥሩ ነው፡፡ ለኢትዮጵያ ቀናዒ ከሆንን ብዝሃነትን ማክበር አለብን፡፡ ይህ ካልሆነ ግን የፉክክር ቤት ሳይዘጋ ያድራል እንዲሉ የምንጮኽላት ኢትዮጵያ ህልም ሆና ትቀራለች፤ ኢትዮጵያ ህልም ከሆነች ራዕያችን ሁሉ ህልም ሆኖ ይቀራል፡፡

    አባቶች በደም እና በአጥንት ያስረከቡንን ውድ አገር እኛ ደግሞ በጭብጨባ እያፈረስን ለን አሳፋሪ ትውልዶች መሆናችን ያሳዝናል፡፡

    ለአፍታም ቢሆን በአገር አልባነት ውስጥ የእያንዳንዳችን ህይወት ምን እንደሚመስል እናስብ፤ በፈረሰ አገር ውስጥ፡-
    ስራ የለም! ቤተሰብ የለም! ልጅ ወልዶ መሳም የለም! መንፈሳዊ ህይወት የለም! ቤተ ክርስቲያን፣ መስጊድ የለም! ሳቅና ጨዋታ የለም! ደመወዝ የለም! ቢራ የለም! ጫት መቃም የለም! መስከርም ሆነ መመርቀን የለም! ጮማ መቁረጥ የለም! ወጥቶ መግባት የለም! ምንም የለም

  • The Ethiopian Army at a Conceptual Crossroad?


    By: Habtamu Girma Demiessie (Jigjiga University)

    Note to readers:- Considerable portion of narratives in this article were adopted from a Book : The Cruces of Post-1991 Ethiopia Politics (Page 85-89, authored by Habtamu Girma & published in December, 2017

    What Justify the Reform Process in the Army?

    One of the foremost tasks of the Abiy government has been to undertake massive reform in the army the security apparatus of the state. The reform process has taken almost two years, and it was declared the mission accomplished. But what triggered the reform process is an important question not just to justify the reform agenda in the army, but also to understand the future course of action in this key department of state.

    The Role of Armed Forces in the Revolutionary Democratic Government

    Since it reorganized in the year 1995, the institutionalization & workings of the Ethiopian army has remained under the umbrella of revolutionary democratic concept. Revolutionary democrats advocate the need to adopt the western way of

    building armed forces.
    According to revolutionary democratic teachings, the army of countries in Western world, though free from politics, in addition to defending the sovereignty of their respective country, stands to defend the western values.

    Therefore, the army, in addition to safeguarding the sovereignty of Ethiopia, should stand to defend the principles and values of revolutionary democracy. Moreover, the army should be built up on the principle of realizing the fair representation of nations, nationalities and people of Ethiopia.

    This is a note on how revolutionary democracy understood the essence of army and the role of armed forces:-
    “…..under a multi-party system, the defense force cannot continue as the army of the EPRDF-it has to be the army of the state……but severing its direct links with EPRDF does not mean abandoning its revolutionary democratic character. Various bourgeoisie armies do not have direct organizational ties or commissars, yet to they could shape in any form for any task the bourgeoisie desire them to fulfill. So we need to gain sufficient experience in how to organize our defense force to carry out the required revolutionary democratic tasks through indirect ties just as in the case of the bourgeoisie armies. Thus although it became free and neutral in appearance, the army will be revolutionary democratic in content and protect the constitution and the rights of the masses.”
    (Source: Revolutionary democracy document disseminated to EPRDF members in 1997 (1985 E.C) to depict principles and directions as to how to move on to meet revolutionary democratic political, social and economic goals)

    Overall, while revolutionary democracy teaches the need to detach the armed forces from the party membership, at the same time it connotes for armed forces adhere themselves to the revolutionary democratic principles and goals.

    However, this depiction is ambiguous, and in many ways open room for critics that propagates hesitations against the professionalism and independence of the army from political influence of the ruling EPRDF.

    How important the Reform Process in Depoliticizing the Army ?

    Today, when the Abiy Ahmed government declared the army has depoliticized in its mission and role, there remains one issue hanging over. That is, the pillars of the reform agenda were not disclosed to public.

    Though all secrets of the state attributed to national defense forces may be understandable, the Ethiopian populace still requires on the principles the army refurbished.

    The people of Ethiopia have a right to question and get answer if the reform process ably insulate the institutionalization of the army from any political interests, if any.

  • እየተንሰራፋ የመጣው የኩላሊት ህመም ከጤና ባሻገር የፖለቲካል-ኢኮኖሚ ገጽታ ይኖረው ይሆን?

    ሀብታሙ ግርማ
    ጥር 5 ቀን 2012 ዓ.ም
    ጅግጅጋ፣ ኢትዮጵያ



    በኢትዮጵያ የጊዜው አሳሳቢ የጤና እክል የኩላሊት ስራውን የማቆም በሽታ (End-Stage Renal Disease (ESRD) ነው። በሽታው በአብዛኛው በከተማው የኢትዮጵያ ማህበረሰብ፣ በተለይም አምራች የሰው ሀይል ክፍልን በስፋት እያጠቃ ይገኛል።

    አንባቢያን የህመሙ ምክንያቶች፣ ምልክቶች፣ የህክምና አማራጮች፣ እና የጥንቃቄ ምክር ከሚከተለው ሊንክ ሊያገኙ ይችላሉ፦ https://www.kidneyfund.org/kidney-disease/kidney-failure/

    የጤና ባለሙያ ስላልሆንኩ ስለጉዳዩ ትንተና መስጠት አልችልም። ነገር ግን በአጭር ጊዜ በሽታው አጣዳፊ የማህበረሰብ ጤና እክል ደረጃ የመድረሱ ነገር ከጤና ባለፈ የፖለቲካል-ኢኮኖሚ ገጽታ ይኖረው ይሆን የሚል ጥያቄን አጭሮብኛል።

    በእርግጥም መንግስት እና ለመንግስት ቅርበት ያላቸው ነጋዴዎች ባለፉት አመታት በምግብ እና ምግብ ነክ ምርቶች እንዲሁም በመድሃኒት ንግድ ላይ በስፋት መሳተፋቸው በምርቶቹ ጥራት ቁጥጥር ላይ የራሱ አሉታዊ ተጽዕኖ እንደሚኖረው እገምታለሁ። ይህም ማህበረሰቡን እንደ ኩላሊት ያሉ ገዳይ በሽታዎች ተጋላጭ የሚሆንበትን ዕድል ማስፋቱ የማይቀር ነው።

    ከዚህ አንጻር እነዚህ ከታች የማነሳቸው ነጥቦች ማየት
    ያሻል፦

    በሽታው እንዲህ በአጭር ጊዜ የመንሰራፋቱን ጉዳይ መንግስት ጉዳዩ በሚፈልገው ልክ ምላሽ ያለመስጠቱ ምክንያት ምን ይሆን?

    ስለ በሽታው ማህበረሰባዊ ግንዛቤ ከማስጨበጥ ይልቅ ወ
    ወይም ከመከላከል ይልቅ ለማከም የሚደረገው ሩጫ ጎልቶ የመታየቱ ነገር ቢፈተሽ፤ ከዚህ አንጻር የዲያሊሲስ ህክምና ውድነት ህክምናው እንደ ቢዝነስ እድል የመጠቀሙ ነገር አዝማሚያ ይኖራል።

    መንግስት የአገር ድንበርን ለመጠበቅ ሰራዊት አሰልጥኖ እንደሚያሰማራው ሁሉ ዜጎቹን እንደ ኩላሊት ህመም አይነት ገዳይ በሽታዎች የመጠበቅ ግዴታ አለበት። ከዚህ አንጻር በሽታው በአመጋገብ ስርዓት እና/ወይም መሰረታዊ የምግብ ማዘጋጃዎች እንደ ዘይት፣ ቅመማ ቅመሞች፣ የምግብ ማሸጊያ እቃዎች፣ የምግብ እና ምግብ ነክ እቃዎች የምርት ጥራት፣ የአገልግሎት ዘመን ክትትል፣ የሚጓጓዙበት እና የሚከማቹበት ሁኔታ ተገቢው ክትትል እና ቁጥጥር መደረግ አለበት።

  • Donald Trump Wrongly Understood !

    Habtamu Girma
    January 11 2020
    Jigjiga, Ethiopia


    In this report by BBC (linked below), I think Trump is wrongly understood. BBC’s report linked Trump’s speech with the Ethio-Eritrea deal. One can find the report via this link:-https://www.bbc.com/news/world-africa-51063149?ns_mchannel=social&ns_source=facebook&ocid=socialflow_facebook&ns_campaign=bbcnews&fbclid=IwAR2419UPhwEeh6nXoC4xi4MnnHvqXa78LCy7_Ev-42gjb3fGEKymG3TwWXU&fbclid=IwAR2CiCjS6NeMJdyprzaadX5i_hqXxSo273HUCmj4TwJRJE_SzWLKbncPmm4

    Trump was Referring about Internal Political Problem in Ethiopia

    As to my inference, Trump has said all about Ethiopia (where he rather referred the country not by name but by its leader, who won this year’s Nobel Peace Prize). There is nowhere Trump referred Eritrea, even indirectly.

    But, what was the problem he referred about Ethiopia? How he managed to resolve the problem? With whom did Trump made a deal?


    What was the problem he referred about Ethiopia?

    As to my inference, the problem he mentioned was the internal political problem surfaced in Ethiopia before three years. According to him, the danger Ethiopia faced was a risk of collapse, and he made a deal to save the country.


    How Trump managed to Resolve the Problem ?

    I understand Trump’s speech in a sense that he played a role to have blocked the inevitable civil war in Ethiopia due to widening rift within EPRDF.


    With whom Trump made deal?

    For me,the deal Trump referred was a deal broken to resolve the two rival camps emerged within EPRDF, the reformist camp against the old guard (TPLF and its affiliates within EPRDF).And from Trump’s speech, one can learn that he was to the side of the reformist camp, resulting the departure of TPLF from central government.


  • THE COST OF POSTPONING THE UPCOMING NATIONAL ELECTION IN ETHIOPIA

    By: Habtamu Girma Demiessie

    Introduction

    The 6th edition of the national election in Ethiopia is scheduled in May 2020. So far, whether to uphold or postpone the time of election is subjected to debate. In this regard, the political pundit active in the country are divided in to two camps.
    The first camp, which is spearheaded by the seasoned academic and politician, Birhanu Nega (Prof.), insists the election time should be rescheduled. The second camp stands for a timely election to hold. This camp is filled by political bigwigs, the likes of Tigray People Liberation Front (TPLF), The Amhara National Movement (NAMA), Oromo Liberation Front (OLF) and the Oromo Federalist Congress Party (OFC).
    The incumbent Prosperity Party has been silent on its stance in this regard. But, its silence has broken just days before, when it held its first executive committee meeting (since EPRDF held a merger with its Satellite Parties to form Prosperity Party late October)
    At least at this moment, just looking the relative influence of the two camps, the camp in support of a timely election is overwhelming. This is perhaps after the Prosperity Party (PP) executive committee expressed its stand on the election to hold in time.
    But, election is not an end, it is only a means to ascertain national consensus via erecting a legitimate government. In some exceptions, where the unity of a country is at its fragile, elections would not be a cure to result a stable politics and government, but otherwise.


    Which Way is better for Ethiopia: Upholding or Postponing Election Schedule?

    Ethiopia is eying for its national election in this May 2020. With the country at crossroad, the essence of the scheduled election would amount not for the sake of promoting democracy, but beyond to maintain rule of law and national integrity. The cost of upholding or postponing the national election amounts with its inevitable consequences in those regards.

    A fair fetch into the Ethiopian political environment tells the country is suffering from two: legitimacy of government and leadership crisis. Therefore, whether to hold election in time or not should be evaluated in healing those fractures.
    At this point in time, Abiy Ahmed and his circle are giving a temporary but substantive solution for both. But, the move is only feasible up until the upcoming election. Otherwise, the inevitable would show-up.
    Well, in my opinion, the inevitable outcomes of not holding election in time are two: delegitimize the government; and further frustrate the leadership crisis in Ethiopia

    Postponing Election upset Legitimacy of Abiy Ahmeds Government

    The immediate effect of postponing election would subject the legitimacy of Abiy Ahmeds rule. That in turn would be consequential exacerbating the fragile national security of the country. In this regard, political forces/groups from within and outside of the country can use the matter to play their subversive games. It takes to understand that these groups achieve their vested interest only at the peril of a destabilized Ethiopian state.


    Postponing Election would Damage the Charisma of Abiy Ahmeds Leadership

    Since Abiy came to power, his leadership has been fighting against the rampant leadership crisis sweeping across all departments of the Ethiopian society, politics, bureaucracy, security, etc. one aspect of the leadership crisis is inability/incapability of the sizable portion of elite group to seeing the bigger picture and decides accordingly that would add to the welfare of Ethiopian populace. So far, Abiy is leading the country by virtue of its charismatic leadership, helping him amass wide support base from within Ethiopia and the global community. Indeed, Abiy has achieved that dealing with imminent attacks not just against his government, but also to personal safety of him and his circle. Abiy has been fixing the leadership crisis in Ethiopia in his patience and wisdom. In his oratorical speeches, he tirelessly connoted leaders to be thoughtful and pass a grown up decisions in their ventures. In his actions, Abiy has shown the personal pride is below the service of the people he led. In his wise leadership quality, Abiys leadership has been showing remarkable achievements. In his charisma, Abiy reinstated Ethiopias honor to its height in the world history. In my opinion, postponing the election would damage the flourishing leadership charisma of Abiy Ahmeds government. Otherwise, Ethiopia would soon count the cost.
    For one, it hampers the reform process the country is forging under the rule of Abiy Ahmed Ali (PhD). Moreover, postponing election would be a good opportunity for infiltrators that work to weaken the rising support base of Abiy, both within and outside Ethiopia.

    May God Save Ethiopia and its People!!!

  • ABIY IS YET TO BE A TRUE LEADER !!!

    HABTAMU GIRMA
    JANUARY 7 2019
    JIGJIGA, ETHIOPIA



    A TRUE LEADER IS SOMEONE WHO IS BOTH WILLING AND ABLE TO SERVE THE CAUSE OF HIS POWER.

    A TRUE LEADER GOES BEYOND HIS/HER INTEREST, AND SURRENDER OWN EGO FOR THE INTEREST OF PEOPLE WHOM SH/E LEADS.

    A TRUE LEADER IS ONE WHO IS NOT THRIFTY TO PUT FORWARD OTHERS AS HIS/HER REPLACEMENT.

    TIME CREATES ITS OWN MAN, AND THAT IS HOW ABIY AHMED SHOW UP IN THIS TROUBLING TIME TO SAVE ETHIOPIAN STATE.

    BUT, ABIY WILL NOT AND SHOULD NOT STAY ON POWER INDEFINITELY. ETHIOPIA NEEDS MANY OTHER LEADERS LIKE ABIY, WHO ARE COMMITTED TO PRESERVE THE UNITY AND NATIONAL INTEGRITY.

    FOR A WHILE, I AM CERTAIN THAT ABIY AHMED IS A RIGHT MAN IN THE RIGHT TIME TO LEAD.

    SO FAR, ABY IS HEADING IN THE RIGHT TRACK TO BE A TRUE LEADER.

    BUT, I AM YET TO BE SURE IF HE CAN BE PRIVILEGED AS A TRUE LEADER. ONLY TIME TELLS THAT.

    I HOPE ABIY AHMED WILL NOT LOSE IN THIS REGARD

    MAY GOD SAVE ETHIOPIA AND ITS PEOPLE !!!!